Fana: At a Speed of Life!

ሀገራችን በምታልፍበት የሁኔታዎች መውጣትና መውረድ፣ በሙላትና በጉድለት ሁሉ ማመስገን ይገባል -የመካነኢየሱስ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ምዕመናን

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገራችን በምታልፍበት የሁኔታዎች መውጣትና መውረድ፣ በሙላትና በጉድለት ሁሉ ማመስገን ይገባል ሲሉ የመካነኢየሱስ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ምዕመናን ተናገሩ።

ዛሬ ሀገራዊው የምስጋና መርሐ ግብር በአምስት ኪሎ መካነኢየሱስ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ተካሂዷል።

በሃይማኖት፣ በማንነትና በሌሎች ማህበራዊ ፓለቲካ ፈተናዎች አልፈን እዚህ መድረሳችን ትልቅ ዋጋ ስላለው ማመስገን ይገባል  ነው ያሉት አማኞቹ።

ሀገሪቱ በጦርነትና በአየር ሁኔታ ለውጥ ምክንያት የደረሱባትን ፈተናዎች ተጋፍጣ ማለፍ መቻሏን በማሰብ ማመስገን ተገቢ መሆኑን ያነጋገርናቸው የቤተክርስቲያኒቱ ምዕመናን ተናግረዋል።

የዕለቱ የምስጋና መርሐ ግብር በዝማሬ፣ በጸሎትና በእግዚአብሔር ቃል አገልግሎት ተከናውኗል።

በበርናባስ ተስፋዬ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.