Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ማዳጋስካር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መከሩ

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያና ማዳጋስካር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በዛሬው ዕለት በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከማዳጋስካር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራሳታ ራፋራቫቪፊካ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ሀገራቱ በግብርና፣ በቆዳ ውጤቶች እና በቱሪዝም ዘርፍ ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይትም አካሂደዋል።

በመራኦል ከድር

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.