Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በአዳማ ከተማ ተካሄዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አብዱልሃኪም ሙሉን ጨምሮ ሌሎች የክልሉና የአዳማ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

አቶ አብዱልሀኪም በዚሁ ወቅት÷በአደማ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቤት እድሳት አስጀምረዋል።

በተመሳሳይ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚከናወን የህፃናት መዋያ ማዕከል ግንባታም ተጀምሯል።

በክልሉ በተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት12 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል፡፡

በዚህም 46 ነጥብ 6 ቢለየን ብር የሚገመት ሥራ በማከናወን 4 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱ ተገልጿል፡፡

በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳትና ግንባታ፣ የአካባቢ ጽዳት፣ ችግኝ ተከላ፣ የማጠናከሪያ ትምህርትን ጭምሮ በተለያዩ ዘርፎች እንደሚከናወን ተጠቁሟል፡፡

በሌሊሴ ተስፋዬና ኦሊያድ በዳኔ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.