Fana: At a Speed of Life!

አቶ ኦርዲን በድሪ ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላለፉ

 

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ከፍተኛ በሆነ ድምጽ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

ይህንን ተከትሎም የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲሞክራሲያዊ በሆነ ሂደት ህዝቡን ዳግም ለማገልገል ዕድል ማግኘታቸውን በመጠቆም መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸውም ተመኝተዋል።

በተያያዘ አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና አቶ አደም ፋራህ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተደርገው በከፍተኛ ድምጽ ተመርጠዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.