Fana: At a Speed of Life!

በትግራይ ክልል ወደ ልማት ባልገቡ ባለሃብቶች ላይ ርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በትግራይ ክልል በተለያዩ የግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ለመሰማራት መሬት ወስደው ወደ ልማት ያልገቡ 24 ባለሃብቶች ላይ ርምጃ ተወሰደ፡፡ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመሬትና ማዕድን ቢሮ  ሃላፊ አቶ ካልአዩ ገብረህይወት እንዳሉት÷ ርምጃው…

አቶ አረጋ ከበደ በቃሉ ወረዳ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶችን እየመረቁ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ ከ143 ሚሊየን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በተገኙበት እየተመረቁ ነው። ከፕሮጀክቶች መካከልም የመስኖ አውታር፣ የድልድይና የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከላት…

በባቱ ከተማ የጥምቀት በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ተደርጓል

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ባቱ ከተማ የጥምቀት በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል፡፡ በከተማዋ የጥምቀት በዓልን በደምበል ደሴቶች በድምቀት ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉ ነው የተመላከተው፡፡…

ማከፋፈያ ጣቢያው የኢትዮጵያና ጅቡቲን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያጠናክራል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 01፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲጋላ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያና ጅቡቲ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል አስታውቋል፡፡ በተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን…

ዜጎች በአንጀንዳ ማሰባሰብ ሒደት ውስጥ በንቃት የመሳተፋቸው አስፈላጊነት…

በሀገራዊ ምከክር ሂደት ውስጥ ዜጎች በአጀንዳ መልክ የሚያቀርቧቸው ሀሳቦች እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡ ነገር ግን ዜጎች እና ባለድርሻ አካላት በአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደት ውስጥ በንቃት መሳተፋችው ለምን አስፈለገ? የትኞቹን ውጤቶች እንዲያመጣስ ይጠበቃል? 👉 አካታች የሆነ…

አገልግሎቱ ከ443 ሺህ በላይ ጉዳዮችን በማስተናገድ 1 ነጥብ 25 ቢሊየን ብር አገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥር 01፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት አምስት ወራት 443 ሺህ 147 ጉዳዮችን በማስተናገድ ከ1 ነጥብ 25 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ዓለምሸት መሸሻ÷…

በባንኩ የዲጂታል አማራጮች የ5 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር ዝውውር ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ስድስት ወራት በዲጂታል አማራጮች የ5 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር ዝውውር መፈፀሙን አስታወቀ። የባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ ዲቪዥን መርቻንትና ኤጀንት ማኔጅመንት ዳይሬክተር ብሌን ኃይለሚካኤል እንዳሉት÷ባንኩ 30 ሚሊየን…

በአማራ ክልል እስካሁን 83 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ታህሣሥ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ከልል በ2016/17 የምርት ዘመን ከመኸር እርሻ እስካሁን ከ83 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡ በቢሮው የሰብል ልማት ባለሞያ እንዬ አሰፋ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ በክልሉ በመኸር እርሻ ሥራ…

በትግራይ ክልል 13 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በትግራይ ክልል በ2016/17 የምርት ዘመን 13 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተመሰብሰቡን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ ኢያሱ አብረሃ (ዶ/ር) እንደገለፁት÷በምርት ዘመኑ የማስፈፀም አቅምን በማሳደግ…

በክልሉ በ53 ሺህ ሄክታር ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ እንደሚከናወን ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቤኒሻንጉል ጉመዝ ክልል በ53 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ እንደሚከናወን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡ በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ ም/ሃላፊ አቶ አብዱልከሪም ሙሳ እንዳሉት÷ በዘንድሮ በጋ የአፈርና ውሃ ጥበቃ…