Fana: At a Speed of Life!

ከለውጡ በኋላ የሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ከ86 ቢሊየን ዶላር ወደ 205 ቢሊየን ዶላር ከፍ ብሏል – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት (ጂዲፒ) በእጥፍ አድጓል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከም/ቤቱ አባላት ለተነሱ…

የመምህራንን ሕይወት ለማሻሻል መንግስት ተጨማሪ እርምጃዎችን ይወስዳል – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመምህራንን ሕይወት ለማሻሻል መንግስት ተጨማሪ እርምጃዎችን ይወስዳል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ…

የዋጋ ግሽበት ከ30 በመቶ ወደ 23 በመቶ ዝቅ ማለቱን ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዋጋ ግሽበት ባለፈው ዓመት ከነበረበት 30 በመቶ ወደ 23 በመቶ ዝቅ ማለቱን አስታወቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከም/ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች…

ባለፉት 11 ወራት 466 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 11 ወራት 529 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 466 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል፡፡ በዚህም መሰረት፡- 1. ወ/ሮ ሽዊት ሻንካ - የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር 2. ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር 3.…

ም/ቤቱ ነገ ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ…

በፕሪሚየር ሊጉ ሃዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሃዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የሃዋሳ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አሊ ሱሌማን በ3ኛው እና 48ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡ የሊጉ 30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሲቀጥል ቀን 10 ሰዓት ላይ…

ገጣሚ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ገጣሚ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ገጣሚ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ነቢይ ባደረበት ህመም ሕክምና ሲከታተል ቆይቶ ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የደራሲው የቅርብ ቤተሰቦች አስታውቀዋል፡፡ ነቢይ መኮንን በህትመት ሚዲያ…

በአቶ አረጋ ከበደ የተመራ ልዑክ ኮምቦልቻ ከተማ ገባ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ የተመራ ልዑክ ኮምቦልቻ ከተማ ገብቷል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የከተማዋ ከንቲባ መሃመድ አሚን የሱፍን ጨምሮ ሌሎች የዞን የሥራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።…

42 ሆስፒታሎች የአገልግሎት ደረጃቸው እየተሻሻለ መሆኑን ዶ/ር መቅደስ ዳባ ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 42 ሆስፒታሎች የአገልግሎት ደረጃቸው እየተሻሻለ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ፡፡ የጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችና መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ መድረክ ሚኒስትሯ በተገኙበት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተካሂዷል፡፡ በዚሁ…