Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ትስስር ከፍተኛ ሚና ትጫወታለች – አቶ አሕመድ ሺዴ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በቀጣናው ሀገራት ደህንነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ዙሪያ ቁልፍ ሚና ትጫወታለች ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ገለጹ። አቶ አሕመድ በሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ በተደረገ የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም መድረክ ላይ በነበራቸው ተሳትፎ እንደገለጹት÷…

የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገቡ ነው – አቶ አደም ፋራህ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገቡ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል፡፡ በዛሬው…

ሐረር ከተማን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ አበረታች ሥራዎች ተከናውነዋል- ቢሮው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሐረር ከተማንተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ባህል ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ ÷ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉን ባህል ፣ ቅርስና ቱሪዝም ከማስተዋወቅ አንጻር ዘርፈ…

1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶስት ዙር በረራ በተከናወነ በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ሥራ 1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ከተመላሾች ውስጥ 1 ሺህ 98 ወንዶች፣ 79 ሴቶች፣ 3 ጨቅላ ህፃናት  እንዲሁም 228  እድሜያቸው…

ክልሉ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ926 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ926 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታወቀ። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ እሸቱ ጎዴቶ እንደገለጹት÷ የክልሉ የይቅርታ ቦርድ በይቅርታ አዋጅ፣ ደንብና…

በሻምፒየንስ ሊጉ ግማሽ ፍፃሜ ዶርትመንድና ፓሪስ ሴንት ጀርሜይን ይፋለማሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመኑ ቦርሺያ ዶርትመንድና የፈረንሳዩ ፓሪስ ሴንት ጀርሜይን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት ያካሂዳሉ፡፡ ጨዋታው ከምሽቱ 4 ሰዓት በዶርትመንድ ሜዳ ሲገናል ኤዱና ፓርከ የሚካሄድ ሲሆን÷ የመልሱ ጨዋታ…

በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 46 በርሚል ነዳጅ ተያዘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 46 በርሚል ነዳጅ መያዙን የሚዛን አማን ከተማ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር አዳነ አለማየሁ እንደገለጹት÷ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ ከተያዘው ነዳጅ ውስጥ 35 በርሚሉ ናፍታ…

ከ80 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለሚያደርግ የውሃ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሃዋሳ ከተማ ከ80 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የውሃ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል፡፡ አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ ተግባራዊ ከሚደረጉ…

የሰራተኞችን መብትና ጥቅም የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል – ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱስትሪ ሰላምን የማረጋገጥ፣ ምርታማነትን የማሳደግ፣ የሥራ ላይ ደህንነትንና የሰራተኞችን ጥቅም የማስከበር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የዓለም የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ለ49 ጊዜ በዓለም…

የውሃ ማጣሪያ ማሽን ለማምረት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከኢቲዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ እና አፒሞሶ ከተሰኘ የቼክ ሪፐብሊክ ኩባንያ ጋር የውሃ ማጣሪያ ማሽን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት፣ ለመገጣጠምና ለማምረት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የውሃና ኢነርጂ…