Fana: At a Speed of Life!

ለሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና እስካሁን ባገኘናቸው ስኬቶች ሳንረካ ሌት ተቀን መስራት አለብን – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና እስካሁን ባገኘናቸው ስኬቶች ሳንረካ ሌት ተቀን መሥራታችንን መቀጠል ይገባናል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ትናንት የተመረቀውን…

በክልሉ በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ለሚገነቡ የቢሮ ሕንጻዎች የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ7 ማዕከላት በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ ለሚገነቡ የቢሮ ሕንጻዎች የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) እና የክልሉ መንግስት ዋና…

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና 2ኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 1 ሺህ 811 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንዳሉት÷ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀትን…

አባ ገዳ ጉዮ ቦሩ ጉዮ 72ኛው አባ ገዳ ሆነው ተሰየሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አባ ገዳ ኩራ ጃርሶ ስልጣናቸውን ለተከታያቸው በሰላም አስረክበዋል። ተከታዩ አባ ገዳ ጉዮ ቦሩ ጉዮ 72ኛው አባ ገዳ በመሆን ለቀጣይ ስምንት ዓመታት ስልጣናቸውን በሰላም ተረክበዋል። አባ ገዳ ኩራ ጃርሶ 71ኛው አባ ገዳ ሆነው ላለፉት…

72ኛው የቦረና ገዳ ባሊ ስልጣን ርክክብ ሥነ ሥርዓት ዛሬ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 72ኛው የቦረና ገዳ ባሊ ስልጣን ርክክብ ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት ይካሄዳል፡፡ በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የኬንያ ልዑካን ቡድን አባላት እንደሚታደሙ ይጠበቃል፡፡ 72ኛው የቦረና ገዳ ባሊ…

ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) የሃይማኖት አባቶች አንድነትን ለማጎልበት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክሩ ጠየቁ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ትናንት ምሽት ከመርቲ ወረዳ ኢማሞችና አቦምሳ ከተማ ነዋሪዎች ጋር አፍጥረዋል፡፡ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የሃይማኖት አባቶች ለልማት፣ ለሕዝቦች አንድነት እና ለዘላቂ ሰላም መስፈን…

ማንቼስተር ዩናይትድ ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ አርሰናልን ያስተናግዳል። ደካማ የውድድር ዓመት እያሳለፈ የሚገኘውና በሁሉም ውድድር ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ድል ማድረግ…

ኮሚሽኑ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳለጥ ድጋፉን እንደሚያጠናክር ገለፀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ቀጥተኛ የውጪ ኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳለጥ ለባለሃብቶች የሚያደርገውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ኮሚሽነሩ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ…

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር በጁባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሀገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና በቀጣናዊ የጋራ ጉዳዮች ዙሪያ…

በሰቆጣ ከተማ የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ዋግ ኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ በአሮሚያ ክልል መንግስት ድጋፍ የተገነባው ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጠናቅቆ ርክክብ ተደርጓል፡፡ ትምህርት ቤቱ በ206…