Fana: At a Speed of Life!

7 አባላት ያሉት የ“ሿሿ” ወንጀል ቡድን በቁጥጥር ሥር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ አካባቢዎች በተሽከርካሪ በመንቀሳቀስ በተለምዶ “ሿሿ" የተባለውን የስርቆት ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ሰባት አባላት ያሉት የወንጀል ቡድን በቁጥጥር ሥር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በቡድኑ አባላት ላይም ምርመራ እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ…

የከተራ በዓል በባቱ ከተማ ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተራ በዓል በባቱ ከተማ ደምበል ደሴቶች ተከብሯል፡፡ በደሴቶቹ የሚገኘው የገሊላ ካህናት ሰማይ ተክለ ሃይማኖት ታቦትና በደብረ ሲና ደሴት የምትገኘው የቅድስት ማርያም ገዳም ታቦታት ከጫሳ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ጋር ሆነው በጥምቀተ ባሕሩ ያድራሉ፡፡…

የመብረቅ አደጋ ባስከተለው እሳት 9 የቀንድና የጋማ ከብቶች ሞቱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ በመብረቅ አደጋ ምክንያት በተነሳ እሳት ዘጠኝ የቀንድና የጋማ ከብቶች ተቃጥለው መሞታቸውን የዞኑ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በመብረቅ አደጋ ምክንያት በተነሳ እሳት በእስሳቱ ላይ ከደረሰው ጉዳት ባለፈ…

የቀድሞ የአ/አ ከተማ ከንቲባ የፕሮቶኮል ዳይሬክተር እነ ኤልቤቴል ሀብቴ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል 10 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ተፈቀደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀድሞ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የፕሮቶኮል ዳይሬክተር እነ ኤልቤቴል ሀብቴ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል 10 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቀደ። ተጠርጣሪዎቹ የቀድሞ የአ/አ ከተማ…

ርዕሳነ-መስተዳድሮች እና ከንቲባዎች ለጥምቀት በዓል የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ክልሎች ርዕሳነ-መስተዳድሮች እና የከተማ አሥተዳደሮች ከንቲባዎች ለጥምቀት በዓል የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ባስተላለፉት…

አቶ ደመቀ መኮንን ከሳዑዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሳዑዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፈይሰል ቢን ፈርሃን አልሳኡድ ጋር ተወያዩ፡፡ ውይይቱን ያደረጉት በዳቮስ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ጎን ለጎን ሲሆን÷…

የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የህዝባቸውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ እየተቸገሩ ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የህዝባቸውን የልማት ጥያቄ ለመመለስና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ከፍተኛ የሆነ ፈተና እየተጋፈጡና እየተቸገሩ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የልዑካን…

ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ክልሎች ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ-መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው በመልዕክታቸው÷ የጥምቀት በዓል ፍቅርን፣ መተሳሰብን፣…

ምስጢረ ጥምቀት

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዘመነ ኦሪት እንደሚከበረው “በዓለ ዳስ” የአደባባይ በዓል የሆነው “በዓለ ጥምቀት” ምስጢር ብዙ ነው፡፡ ወደ ወንዝ ሄዶ በመጠመቅ ከበሽታ መፈወስም የተለመደ መሆኑን በኢዮብ እና በሶርያዊው ንእማን ታሪክ ላይ ተሠንዶ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ መነሻነት…

ጥምቀት በኢራንቡቲ እንደወትሮው ሁሉ በድምቀት ይከበራል – መምሪያው

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተራ እና የጥምቀት በዓል በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ኢራንቡቲ እንዳለፉት ዓመታት ሁሉ እሴቱን ጠብቆ በሰላም እንዲከበር የዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የሰሜን ሸዋ ዞን ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል፡፡ በዓሉ በስኬት እንዲከበር ለማድረግም…