Browsing Category
የሀገር ውስጥ ዜና
ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም መረጋገጥ በሙሉ ዝግጁነት ላይ ትገኛለች- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም መረጋገጥ በሙሉ ዝግጁነት ላይ ትገኛለች ሲሉ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገለጹ፡፡
ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ሞተራይዝድ ሻለቃ የደረሰበትን ዝግጁነት ደረጃ…
በአማራ ክልል የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን በቅንጅት ለመፍታት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት የጋራ ግብን መሠረት በማድረግ የሰላምና የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን በቅንጅት ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
ለሁለት ቀናት የሚቆይ በወቅታዊ የሰላምና…
የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራ ሠራዊቱ ባለበት ሁሉ ይከናወናል- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሠራዊቱ በሚገኝበት ሁሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ፡፡
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ በመከላከያ የሎጂስቲክ ዋና መምሪያ…
በሻንጋይ ኤክስፖ የዲጂታል ኢትዮጵያ መርሐ ግብርን እውን ለማድረግ ልምድና ተሞክሮ አግኝተናል – ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻንጋይ ኤክስፖ ኢትዮጵያ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የዲጂታል ኢትዮጵያ መርሐ ግብርን እውን ለማድረግ የሚያግዝ ልምድና ተሞክሮ ማግኘት ችለናል ሲሉ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ገለፁ፡፡
በቻይና - ሻንጋይ ከተማ በመካሄድ…
የፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ሰኔ 24 ማካሄድ ይጀምራል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሰኔ 24 እና 25 ቀን 2016 ዓ.ም 6ኛ የፓርላማ ዘመን 3ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን እንደሚያካሂድ ተገለፀ፡፡
ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ለሁሉም የምክር ቤቱ አባላት የፊሲካል ፌዴራሊዝም መሰረታዊ…
የቀጣዩ ዓመት የትምህርት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2017 ትምህርት ዘመን የትምህርት ንቅናቄ ማስጀመሪያ ክልላዊ መድረክ እና የፈጠራ ሥራ ዐውደ-ርዕይ በሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
"በሣይንስና ቴክኖሎጂ የታከለ ትውልድ ለሀገራችን ብልፅግና" በሚል መሪ ሐሳብ…
የስራ እድልን ለማስፋት የሚያግዝ ሥምምነት ተፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ግራቪቲ ግሩፕ ከተባለ መቀመጫውን በተባበሩት አረብ ኢምሬት ካደረገው ድርጅት ጋር ለዜጎች የስራና የስልጠና እድል ለማስፋት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
በስምነቱ መሠረት ዜጎች በህትመት ዘርፍ ሠልጥነው የሥራ ዕድል…
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ተጠየቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ አሳሰቡ።
የምክር ቤቱ አባላት የተሳተፉበት የምክክር መድረክ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ አፈ-ጉባዔው…
ለሸነን አፍሪካ ፌስቲቫል የሚሳተፉ እንግዶች አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሸነን አፍሪካ ፌስቲቫል የሚሳተፉ የክብር እንግዶች አዲስ አበባ ገብተዋል።
የሸነን አፍሪካ ፌስቲቫል ሳምንት ከነገ ጀምሮ እስከ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
በፌስቲቫሉ የውጭ ሀገራት የእግር ኳስ…
ግብይት ሳይፈጸም ደረሰኝ በመሸጥ ከ3 ቢሊየን ብር በላይ የታክስ ጉዳት በማድረስ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተከሰሱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18 የንግድ ዘርፎች ፈቃድ በመውሰድ ግብይት ሳይፈጸም ደረሰኝ በመሸጥ ከ3 ቢሊየን ብር በላይ የንግድ ትርፍና የተጨማሪ እሴት ታክስ ጉዳት በማድረስ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተከሰሱ።
የፍትሕ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ…