Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ታዬ ከተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ረዳት ዋና ጸሐፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ረዳት ዋና ጸሐፊ ሊ ጁን ሁዋን ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸው የዘላቂ ልማት ግቦችን አፈጻጸም ለማፋጠንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ…

ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጋዜጠኞች ሙያቸውን እና ሕግን እንዴት መከተል እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በሚል መሪ ቃል በሚዲያ…

በህገ ወጥ መንገድ ግለሰቦችን ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ወንጀል የተከሰሱ በእስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በህገ ወጥ መንገድ ሰባት ግለሰቦችን በጅቡቲ በኩል ወደ ውጭ ሀገር በመላክ የወንጀል ድርጊት የተከሰሱ በጽኑ እስራት እና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል። ተከሳሾች ነኢም አወል እና ሰይድ (ሳዲቅ) ሀሰን የተባሉ ደላሎች ናቸው። በፍትህ…

 ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡለትን ሹመቶች አጽድቋል፡፡ በዚሁ መሰረት 1ኛ. አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና…

የኑሮ ውድነት እንዳይባባስ በትኩረት እየተሰራ ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ምክንያት የኑሮ ውድነት ችግሮች እንዳይባባሱ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ፡፡ ከንቲባዋ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ…

የባህር ሰሌዳ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ የዓለም ዓይንና ጆሮ በባህር ሞገዶች እና በመርከቦች ድምፅ ላይ ሆኗል። የመጫወቻ ካርዱን የሚዘውሩት ኃያላንም በጥቅም ግጭቶች እየተላተሙ ይገኛሉ። የዓለም ኢኮኖሚ ደም ሥር የሆነው ነዳጅ ዛሬም እንደ ትናንቱ ወሳኝ ነው፡፡ ሆርሙዝ…

የአፍሪካ ሀገራት ከኢትዮጵያ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ተሞክሮ ሊወስዱ ይገባል – ኤሊቪስ ሚሺላ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመጀመሪያው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS2026) በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ለመሳተፍ አዲስ አበባ የሚገኘው ኬኒያዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ ኤሊቪስ ሚሺላ እንዳለው÷…

በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተዋል

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተዋል አሉ፡፡ በጅማ ከተማ በ3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ወጪ…

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአፋህድ አባላት ጋር ተወያየ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሰላም አማራጭን ከተከተሉ 153 የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋህድ) አመራር እና አባላት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለሶስት ቀናት ተወያይቷል። በአማራ ክልል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የአፋሕድ…

አዲሱ የተፅዕኖ ድምፅ የሆነው ማህበራዊ ሚዲያ የአፍሪካውያንን ተስፋ እንዲያሳይ …

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ አህጉራዊ አንድነትን ለመገንባት የሚወሰድ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው አሉ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ፡፡ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ…