Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

በክልሉ የተጀመሩ መሠረተ-ልማቶች ግንባታን በዚህ ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የተጀመሩ መሠረተ-ልማቶች ግንባታን በዚህ ዓመት መጨረሻ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለፁ፡፡ የክልሉ መንግሥት ለሕዝቡ የመሠረተ-ልማት ጥያቄዎች…

ሸገር ከተማ የሐይማኖቶች እኩልነት መገለጫ ናት – ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ በሸገር ከተማ አሥተዳደር ኮዬ ፈጨ ክፍለ ከተማ የጎዳና ላይ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ተካሄደ፡፡ በመርሐ-ግብሩ ላይም፤ የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛን (ዶ/ር) ጨምሮ የከተማዋ እና የክፍለ ከተማው አመራሮች…

በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ3 ሺህ በላይ ወገኖች ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 3 ሺህ 416 ኢትዮጵያውያን በዚህ ሣምንት ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሴቶችና ማኅበራዊ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ እነዚህ ወገኖች ወደ ሀገራቸው የተመለሱት በሳምንቱ ውስጥ በተደረጉ ዘጠኝ በረራዎች…

ዘመቻ አንድነት በሚል በአማራ ክልል ትንኮሳ ለመፈፀም የሞከረው ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ቡድን ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በብርጋዲየር ጄኔራል ምግበይ ኃይለና ግብረ አበሮቹ አደራጅነትና አይዞህ ባይነት ዘመቻ አንድነት በሚል ስያሜ በተለያዩ የአማራ ክልል ወረዳዎች ትንኮሳ ለመፈፀም የሞከረው ፅንፈኛው ቡድን ላይ እርምጃ መውሰዱን መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ፡፡…

የኢትዮ-አሜሪካን ዘርፈ-ብዙ ትብብር ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እና አሜሪካን ኢኮኖሚያዊ ጨምሮ ዘርፈ-ብዙ ትብብሮች በይልጥ ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሄደ፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ሰመሪታ ሰዋሰው ከአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ የአፍሪካ ፖሊሲ ከፍተኛ ፕሮፌሽናል ስታፍ አባል ከሆኑት…

ጤፍን ከባዕድ ነገር ጋር ቀላቅለው እንጀራ ለገበያ ሲያቀርቡ የነበሩ 84 ግለሰቦች በቁጥጥ ሥር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሐዋሳ ከተማ አሥተዳደር ጤፍን ከባዕድ ነገር ጋር ቀላቅለው እንጀራ ጋግረው ለገበያ የሚያቀርቡ 84 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአሥተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ ኮማንደር መልካሙ አየለ እንደገለጹት፤ በዋናነት…

ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ዘርፍ በሰፊው ሊሠራበት እንደሚገባ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከፍተኛ ለውጥ እያሳየ የሚገኘው የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ዘርፍ በሰፊው ሊሠራበት ይገባል ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡ ሚኒስትሯ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባጋሩት ጽሑፍ፤ የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ባለፉት አራት ዓመታት በክልሉ…

የምስራቅ አፍሪካ የጥበባትና ባህል ፌስቲቫል የቀጣናውን ሀገራት ትስስር ያጠናክራል – ሚኒስትሮች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የጥበባትና ባህል ፌስቲቫል የቀጣናውን ሀገራት ትስስር ለማጠናከር የላቀ ሚና እንዳለው የአፍሪካ ሀገራት ባህልና ስፖርት ሚኒስትሮች ገለጹ። 2ኛው የምስራቅ አፍሪካ የጥበባትና ባህል ፌስቲቫል "ጥበብና ባህል ለቀጣናዊ ትብብር"…

የቻይና ባለሀብቶች በተለያዩ አማራጮች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ከሆኑት ቼን ሀይ ጋር በሁለትዮሽ የሥራ ስምምነት ላይ በአርባምንጭ ከተማ ተወያይተዋል፡፡ በዚሁ ወቅት ርዕሰ መሥተዳድሩ እንዳሉት፤ በክልሉ በርካታ የቻይና…

ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድ ትሥሥር ማጠናከር እንደምትፈልግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ሰመሪታ ሰዋሰው በኢትዮጵያ የፊንላንድ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን እና የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በዚሁ ወቅትም፥ ፊንላንድ በተለይም በትምህርት ዘርፍ ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ድጋፍ ሚኒስትር…