Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ስፓርት

የኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ሲደረጉ ፉልሀም ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም ብራይተን ከኖቲንግሃም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ ቀን 9 ሰዓት ከ15 ላይ በማርኮ ሲልቫ የሚመራው ፉልሀም በሜዳው ክራቨን ኮቴጅ ክሪስታል ፓላስን…

ቡካዮ ሳካ ከረዥም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ልምምድ ተመለሰ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርሰናሉ ወሳኝ ተጫዋች ቡካዮ ሳካ ከሶስት ወራት ጉዳት በኋላ ወደ ልምምድ መመለሱ ተነግሯል፡፡ ተጫዋቹ ከቡድኑ ጋር ልምምድ መስራቱ የተገለጸ ሲሆን፥ አርሰናል በቻምፒየንስ ሊጉ ከሪያል ማድሪድ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡…

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ የደጋፊዎች ድምጽ አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሰሞኑን በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ1 ሺህ 500 ሜትር ርቅት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቷ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ የደጋፊዎች ድምጽ አሸናፊ ሆናለች፡፡ የዓለም አትሌቲክስ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ ባጋራው መረጃ፤ ከደጋፊዎች ባሰባሰበው ድምጽ…

አርጀንቲና አራት ጨዋታ እየቀራት ወደ ዓለም ዋንጫ አለፈች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ አሜሪካ ሀገራት የ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከብራዚል ጋር ጨዋታዋን ያደረገችው አርጀንቲና 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች። የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ዩሊያን አልቫሬዝ፣ ኢንዞ ፈርናንዴዝ፣ አሌክሲስ ማክ አሊስተር እና ጁሊያኖ…

ሴፕ ብላተር እና ሚሼል ፕላቲኒ ከቀረበባቸው ክስ በድጋሚ በነፃ ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ የፊፋ ፕሬዚዳንት ሴፕ ብላተር እና የቀድሞ የዩኤፋ ፕሬዚዳንት ሚሼል ፕላቲኒ ከቀረበባቸው በፊፋ የፋይናንሺያል የስነ ምግባር ጥሰት ክስ በነፃ መሰናበታቸው ተገልጿል። ሁለቱ የቀድሞ የእግር ኳስ ከፍተኛ ኃላፊዎች በፈረንጆቹ 2011 ላይ…

ሸገር ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ አንድ እየተሳተፈ የሚገኘው ሸገር ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። ዛሬ የምድብ 18ኛ ጨዋታውን ያደረገው ሸገር ከተማ እንጅባራ ከተማን 5 ለ 1 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ ነጥቡን 45…

ፔፕ ጋርዲዮላ በማንቼስተር ሲቲ…

ማንቼስተር ዩናይትድን በታሪክ ማማ ላይ የሰቀሉት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ፔፕ ጋርዲዮላ በፈረንጆቹ 2016 ወደ ማንቼስተር ሲቲ ሲመጣ ስለ ስፔናዊው አሰልጣኝ ተጠይቀው የሰጡት መልስ "ይህ ቡንደስ ሊጋ ወይም ስፔን ላሊጋ ሳይሆን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነው" የሚል ነበር፡፡ ይህ ምላሻቸውም ፔፕ በሁለቱ…

በቻይና ናንጂንግ የተሳተፈው ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና ናንጂንግ በተካሄደው 20ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል። የልዑካን ቡድኑ አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የጀግና አቀባበል…

ኢትዮጵያ በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና ናንጂንግ እየተካሄደ ባለው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች የ3000 ሜትር ፍጻሜ በአትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አማካኝነት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ብርቄ ኃየሎም አምስተኛ ወጥታለች። ከቀኑ 8…

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና ናንጂንግ እየተካሄደ በሚገኘው 20ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ። በዚህ መሰረትም ከቀኑ 8 ሰዓት ከ15 ላይ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር…