Fana: At a Speed of Life!

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ካቢኔ አባላት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። አቶ አሻድሊ ሀሰን በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት÷ ኢትዮጵያውያን ያለ ልዩነት በሚያደርጉት አስደናቂ ድጋፍ ግድቡ…

በሐረሪ ክልል የተማሪዎች ምዝገባ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበበ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ እየተከናወነ መሆኑን የሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ ምዝገባው በክልሉ በገጠር እና ከተማ በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መገለጹን…

የመድሐኒት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ – አቶ ጥላሁን ከበደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጤና ተቋማት ላይ የሚታየውን የመድሐኒት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት 2ኛ ዙር የፓርላማ አባላት እና…

በፓሪስ ኦሊምፒክ የተሳተፈችው አትሌት ፍቅረኛዋ ባደረሰባት ጥቃት በእሳት መቃጠሏ ተሰማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዑጋንዳዊቷ የማራቶን ሯጭ ርብቃ ቼፕቴጌ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በፍቅረኛዋ በደረሰባት ጥቃት አብዛኛው የሰውነቷ ክፍል በእሳት መቃጠሉን ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በአትሌቷ  እና ፍቅረኛዋ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ ቤንዚን በላይዋ ላይ…

የአየር መንገዱ አስመራ ቅርንጫፍ የሂሳብ ደብተር መታገዱ በረራ ለማቆም አንዱ ምክንያት ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስመራ ቅርንጫፍ የሂሳብ ደብተር ሙሉ ለሙሉ መታገዱ በረራ ለማቆም አንዱ ምክንያት እንደሆነ ተገለጸ፡፡ አየር መንገዱ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ማቋረጡን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙኃን…

የሩሲያው ፕሬዚዳንት ሞንጎሊያን  እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኤሲያዋን ሀገር ሞንጎሊያን እየጎበኙ ነው፡፡ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በአለፈው ዓመት የዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት በፕሬዚዳንት ፑቲን ላይ የእስር ማዘዣ ማስተላለፉ የሚታወስ ሲሆን÷ ከዚሁ…

ኢትዮጵያ በፓራሊምፒክ 3 ሜዳሊያዎች በማግኘት ተሳትፎዋን አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንሳይ ፓሪስ በተካሄደው 17ኛው የፓራሊምፒክ ውድድሮች ኢትዮጵያ 2 የወርቅና 1 የብር ሜዳሊያዎችን በማግኘት ተሳትፎዋን አጠናቅቃለች። በዚሁ መሠረት አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የጭላንጭል (T-13) እና ያየሽ ጌቴ በ1…

አሜሪካ የሁቲ አማጺያን የሚሳዔል ማስወንጨፊያ ማዕከልን አወደመች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀይ ባህር ላይ የነበሩ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ጥቃት ከደረሰ በኋላ አሜሪካ የሁቲ አማጺያን ሚሳኤል የሚያስወነጭፉባቸውን ማዕከል አወድማለች፡፡ የአሜሪካ ጦር በየመን በሁቲ አማጺዎች ቁጥጥር ስር ባለዉ አካባቢ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ቡድኑ…

በሲዳማ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ ምዕራፍ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በሲዳማ ክልል በሐዋሳ ከተማ ሲያከናውነው የነበረው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ አጠናቋል። የክልሉን አጀንዳ ያደራጁ ወኪሎችም አጀንዳቸውን ለሀገራዊ ምክክሩ አስረክበዋል። በሲዳማ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ…