Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል 93 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት 93 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 4 ሺህ 316 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡ የቢሮው ሃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ እንዳሉት÷በበጀት…

ዶ/ር መቅደስ የወባ በሽታን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ተግበራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳሰቡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የወባ በሽታ ሥርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተከናወኑ ያሉ ተግበራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡ የጤና ሚኒስቴር የወባ ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጣር እየተካሄደ ያለውን ተግባራት አስመልክቶ…

የፊፋ ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጆያኒ ቪንቼንዞ ኢንፋንቲኖ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) 46ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ  ነው ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ የገቡት፡፡…

በአዲስ አበባ መርካቶ ሸማ ተራ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ መርካቶ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ…

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን እድሳት ሕንጻን መርቀው ከፈቱ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የታደሰውን የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሕንጻ መርቀው ከፍተዋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ…

370 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 370 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ተመላሾቹ 329 ወንዶች፣ 39 ሴቶችና 2 ጨቅላ ህጻናት ሲሆኑ ÷ ከእነዚህ መካከልም 16 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ…

በማንዱራ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ወደ ሰላም መምጣታቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ለሰላም ቅድሚ በመስጠት ወደ ወረዳ ማዕከል ገብተዋል። ለሰላም ተመላሾቹ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ም/አፈ-ጉባዔ መለሰ ኪዊ፣ የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አትንኩት ሽቱ…

የኢትዮጵያና የኦስትሪያ የቢዝነስ ፎረም ነገ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና የኦስትሪያ ቢዝነስ ፎረም ነገ እንደሚካሄድ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር)÷ በፎረሙ የሁለቱ ሀገራት ግዙፍ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉና አጋጣሚው የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ…

ለፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል የሞተር ሳይክል ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የቻይናው ‘ሳንፖሎ የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል’ አምራች ኩባንያ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል ሞተር ሳይክሎችን በድጋፍ አበረከተ፡፡ ሞተር ሳይክሎቹ በማዕከሉ ሆነው ከጉዳታቸው እያገገሙ ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት አገልግሎት…

በሰፊ መዳረሻ የላቀ አገልግሎት ለመስጠት እየሠራሁ ነው- የኢትዮጵያ አየር መንገድ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በተቀላጠፈ እና በሰፊ መዳረሻ የላቀ አገልግሎት ለመስጠት እየሠሩ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው አስታወቁ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው የአየር መንገዱን የካርጎ ሎጅስቲክስ አገልግሎት በተመለከተ በሰጡት…