Fana: At a Speed of Life!

ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ግለሰቦች እስከ ቅዳሜ ድረስ እንዲመልሱ አሳሰበ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ወይም ወደተለያየ ሂሳቦች ያስተላለፉ ግለሰቦች እስከ መጪው ቅዳሜ ድረስ በፈቃዳቸው እንዲመልሱ አሳስቧል፡፡ ሰሞኑን ባንኩ ካጋጠመው የሲስተም ችግር ጋር ተያይዞ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ…

በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያ የነሐስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች የመሰናክል ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት ሎሚ ሙለታ የነሐስ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡ አትሌቷ 9 ደቂቃ 26 ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው 3ኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው፡፡ እንዲሁም አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ እና…

መሬት እናሰጣለን በማለት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ተቀብለዋል የተባሉ የቀድሞ የመዲናዋ ሰራተኞች ጥፋተኛ ተባሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባዶ መሬት እናሰጣለን በማለት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ሙስና ተቀብለዋል የተባሉ የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3 ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ተባሉ። ተከሳሾቹ 1ኛ የአራዳ…

ሩሲያ የታገደው ሀብቷን በተመለከተ የአውሮፓ ህብረት ዕቅድን አወገዘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ የታገዱ የሩሲያ ንብረቶች ላይ የአውሮፓ ህብረት የያዘውን ዕቅድ አውግዛለች፡፡ ክሬምሊን የአውሮፓ ህብረት የውጭ ፖሊሲ ኃላፊ ጆሴፍ ቦሬል እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ የሩሲያ ንብረቶችን ለዩክሬን የጦር መሳሪያ መግዣነት እንዲውሉ ያቀረቡት ሀሳብ…

ኅብረቱ ጥቂት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የፈጸሙትን ድርጊት አወገዘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት ጥቂት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የፈፀሙትን ያልተገባ ድርጊት አወገዘ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሠራሩን ለማዘመን ባደረገው እንቅስቃሴ በተፈጠረ ስህተት የገንዘብ…

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ለሥራ ጉብኝት ጁባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የተመራ ልዑክ ለሥራ ጉብኝት ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል። ልዑኩ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ያቀረበለትን ግብዣ ተከትሎ ነው ለሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት ጁባ የገባው፡፡ የልዑካን ቡድኑ…

በሴቶች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት መንስኤን በመለየት መስራት አለብን – ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሴቶች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የችግሮቹን መንስኤ በመለየት መስራት አለብን ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ገለጹ፡፡ በግሪክ አቴንስ እየተካሄደ ባለው የሴቶች የፖለቲካ መሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ያሉት ፕሬዚዳንት…

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህገ ወጥ የማዳበሪያ ስርጭትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት እንደሚጠናከር ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአፈር ማዳበሪያ ዕዳ ለመሰብሰብ እና ህገ ወጥ ስርጭትን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ፡፡ በክልሉ የዞኖች እና የልዩ ወረዳዎች የሠላምና…

የአየር ሃይል አመራሮችና አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ አየር ሃይል አመራሮች፣ አባላትና ሲቪል ሰራተኞች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል፡፡ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች÷ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የኢትዮጵያዊያን የተጋድሎ ታሪክ መዘከሪያ ብቻ ሳይሆን ለአዲሱ ትውልድ የሀገር ፍቅር ስሜትን የሚፈጥር…