Fana: At a Speed of Life!

በሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው እና አብዲ ሞሃመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) መዝገቦች ቀርበው የነበሩ ክሶች ተቋረጡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍትህ ሚኒስቴር በሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው እና በአብዲ ሞሃመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) መዝገቦች ቀርበው የነበሩ ክሶች ለህዝብ ጥቅም ሲባል እንዲቋረጡ መወሰኑን አስታወቀ። በእነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው መዝገብ ስር ያሉ ተከሳሾች በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ…

አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከኬንያ አቻቸው ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከኬንያ አቻቸው ሙሳሊያ ሙዳቫዲ (ዶ/ር) ጋር ተወያዩ፡፡ ውይይታቸውም በሁለትዮሽና ቀጣናዊ የጋራ ፍላጎቶች ላይ ትኩረት ያደረገ እንደነበር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከ600 ሺህ የሚበልጡ ዘመናዊ ቀፎዎችን ለአርሶ አደሩ ማድረስ ተችሏል – አቶ ሽመልስ አብዲሳ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016(ኤፍ ቢ ሲ) በበጀት ዓመቱ እስካሁን ከ600 ሺህ የሚበልጡ ዘመናዊ ቀፎዎችን ለአርሶ እና አርብቶ አደሩ ማድረስ እንደተቻለ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ፡፡ አቶ ሽመልስ አብዲሳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷ የለውጡ መንግስት ዓላማ…

በጀልባ ወደ ጣልያን ሲጓዙ የነበሩ 50 ስደተኞች ሕይዎት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀልባ ከሊቢያ ወደ ጣልያን ሲጓዙ የነበሩ 50 ስደተኞች ሕይወት አልፏል፡፡ ይህን የገለጹት በአደጋው ሕይወታቸው ካለፉ ሰዎች ጋር አብረው የነበሩና ከአደጋው የተረፉ ስደተኞች ናቸው ተብሏል፡፡ ከአደጋው የተረፉት 25 ሰዎች መካከል ሁለቱ…

አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከአሜሪካ የሱዳን ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016(ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከአሜሪካ የሱዳን ልዩ መልዕክተኛ ቶም ፔሪሎ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች እንዲሁም በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መምከራቸው ተገልጿል፡፡ አምባሳደር ታዬ…

ኢትዮጵያ ከሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ብሔራዊ ጥቅሟን በሚያስከብር መልኩ ትሰራለች- ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016(ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር ያላትን ግንኙነት ብሔራዊ ጥቅሟን በሚያስከብርና በሚያስቀጥል መልኩ እንደምትሰራ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ አስታወቁ፡፡ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ የተሾሙ የ11 ሀገራትን አምባሳደሮች የሹመት…

ከትግራይ ክልል የተወጣጡ የሕብረተሰብ ተወካዮች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሁሉም የትግራይ ክልል አካባቢዎች የተወጣጡ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍል ተወካዮች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል፡፡ ተወካዮቹ የጋራ የድል ታሪካችን የሆነው የዓድዋ ድል መጪውን ትውልድ በሚያስተምር፣ በሚያስተሳስርና ታሪኩን በጠበቀ መልኩ የዓድዋ…

የዓድዋ ድል መታሰቢያ ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ ለጉብኝት ክፍት ሊደረግ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓድዋ ድል መታሰቢያ ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ ለጉብኝት ክፍት እንደሚደረግ የድል መታሰቢያው ዋና ዳይሬክተር ውባየሁ ማሞ (ኢ/ር) ገለፁ ። የጉብኝቱን ሒደትና የሚጎበኙ ሥፍራዎችን በተመለከተ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም መግለጫ እንደሚሰጥም ዋና…

አቶ አህመድ ሺዴ መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገሪቱ ማክሮ ኢኮኖሚ፣ ሰላም ግንባታና የተፈጥሮ አደጋዎችን በመቋቋም ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የመንግስትና የልማት አጋሮች የጋራ የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የልማት አጋር ድርጅቶች ሃላፊዎች፣…

የአማራ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቃላችንን እናከብራለን! በዘላቂነት እግር እንተክላለን! በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሄድ የቆየው የአማራ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የውይይት መድረክ ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ። ከመጋቢት 2 እስከ 5 ቀን 2016 ዓ.ም በክልሉ…