Fana: At a Speed of Life!

የአለም አቀፍ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በኢትዮጵያ የሚተገብረውን የሰብአዊ እገዛ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአለም አቀፍ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በኢትዮጵያ የሚተገብረውን የሰብአዊ እገዛ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአለም አቀፍ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ማሪያና ስፓልያሪች ጋር…

የልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ወደ 11 ቢሊየን ብር አደገ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ባለፉት ሦስት ዓመታት ከነበረበት 2 ቢሊየን ብር ወደ 11 ቢሊየን ብር ማደግ መቻሉን ባንኩ ገልጿል። ባንኩ በግብርና ዘርፍ ለተሰማሩ ደንበኞቹ 15 ትራክተርና 10 ኮምባይን ሀርቨስተር እንዲሁም…

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ለኬንያውያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ለኬንያውያን 60ኛ አመት የነጻነት ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ፕሬዚዳንቷ በ60ኛው የኬንያ ነጻነት ቀን ላይ በኬንያ ናይሮቢ ተገኝተው በኢትዮጵያ ህዝብ ስም መልዕክት ያስተላለፉ…

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት “ቅኝት” የተሰኘ ትምህርታዊ ገለጻን አስጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የመጀመሪያውን "ቅኝት" የተሰኘ ትምህርታዊ ገለጻን ጅማሬ ዛሬ አብስሯል፡፡ በመድረኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑት የልማት ምጣኔ ሃብት ጄፈሪ ሳክስ (ፕ/ር) በተከፋፈለው አለም ዘላቂ ልማትን በገንዘብ በመደገፍ…

ኢትዮጵያን ወደ ፈጠራና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ለመምራት እየተሰራ ነው – በለጠ ሞላ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያን ወደ ፈጠራ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ለመምራት እየተሰራ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ ዶ/ር ገለጹ፡፡ በማይክሮሶፍት ካምፓኒና በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢትዮጵያን ዲጂታል ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ በሚያስችሉ…

የፋይናንሱ ዘርፍ ማሻሻያዎች ጠንካራ የምጣኔ ኃብት እድገት ለማምጣት ወሳኝ መሆናቸው ተመለከተ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፋይናንስ ዘርፍ እየተደረጉ ያሉ ለውጦች ዘላቂና ጠንካራ የምጣኔ ኃብት እድገት ለማምጣት መሠረት እየጣሉ መሆኑን በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የልማት መርሐ-ግብር ከፍተኛ የምጣኔ ኃብት አማካሪ አሊ ዛፋር ገለጹ። የምጣኔ ኃብት አማካሪው አሊ…

በጎንደር ከተማ 872 ተጠርጣሪዎች የተሃድሶ ሥልጠና ወስደው ሕብረተሰቡን ተቀላቀሉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩ 872 ተጠርጣሪዎች የተሃድሶ ሥልጠና እና የምክር አገልግሎት ተሰጥቷቸው ሕብረተሰቡን መቀላቀላቸውን ኮማንድ ፖስቱ ገለጸ፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ በጎንደር ከተማ…

አዲሱን ‘የዓየር መንገድ ከተማ’ ግንባታ በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አዲሱን ‘የዓየር መንገድ ከተማ’ ግንባታ በአራት ዓመታት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሠራ መሆኑን ገለጸ፡፡ ዓየር መንገዱ “ኤርፖርት ሲቲ” ብሎ የሚጠራውን ግንባታ ለመጀመር ከጫፍ የደረሰው እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት…

የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ማዕድን በመያዝ ወንጀል የተከሰሱት የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ምስክር መሰማት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና የተለያየ ዓይነት ማዕድኖችን በመያዝ ወንጀል የተከሰሱት የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ልደታ ምድብ 8ኛ የገቢዎችና ጉሙሩክ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ምስክር መሰማት ጀመረ። የፍትህ…