Fana: At a Speed of Life!

የረመዷን ጾም ዛሬ ጨረቃ ከታየች ነገ ፣ ካልሆነ ግን ከነገ በስቲያ ይጀምራል – የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ1444ኛው ዓመተ ሒጅራ የረመዷን ጾም ማክሰኞ (ዛሬ) ጨረቃ ከታየች ረቡዕ (ነገ) ፣ ካልሆነ ግን ሐሙስ (ከነገ በስቲያ) እንደሚጀምር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክርቤት አስታወቀ።   ምክር ቤቱ የ1444ኛው ዓመተ ሒጅራ…

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቋል፡፡ በዚህም መሰረት አቶ መምህሩ ሞኬ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ፣ አቶ ከበደ ጋኖሌ የክልሉ የዉሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ…

በጅግጅጋ ከተማ የመጀመሪያው የተስፋ ብርሃን ምገባ ማዕከል ግንባታ ስራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅግጅጋ ከተማ የመጀመሪያው የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ግንባታ ስራ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡   በግንባታ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የሶማሌ ክልል አመራሮች ተገኝተዋል፡፡…

ጠንካራ የፓርቲ ቁመና በመፍጠርና መንግስት በመገንባት የኢትዮጵያን ብልጽግና ዕውን ለማድረግ እየተሰራ ነው – አቶ አደም ፋራህ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብልጽግና ፓርቲ ጠንካራ የፓርቲ ቁመና በመፍጠርና ጠንካራ መንግስት በመገንባት የኢትዮጵያን ብልጽግና ዕውን ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የብልጽግና አመራሮች ስብሰባ…

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የተፈቀደ ካፒታሉ ወደ 221 ቢሊየን ብር ከፍ እንዲል ወሰነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት÷የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በግንባታ ላይ ያሉ መሰረተ ልማቶች እንዲጠናቀቁና የተጠናቀቁት ወደ ስራ እንዲቡ የተፈቀደ ካፒታሉ ወደ 221 ቢሊየን ብረ ከፍ እንዲል ወሰነ፡፡ ሚኒስትሮች ምክር…

አሜሪካ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት “ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈፅሟል” በሚል ያወጣችውን ሪፖርት እንደማትቀበል ኢትዮጵያ ገለፀች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት “በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈፅሟል” በሚል ያወጣውን ሪፖርት እንደማይቀበል የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት…

በዝናብ ወቅት የሚከሰቱ አደጋዎችን ለመቀነስ ሕብረተሰቡ የበኩሉን እንዲወጣ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የበልግ ወቅት ዝናብን ተከትሎ የሚከሰቱ አደጋዎችን ለመቀነስ ሕብረተሰቡ የበኩሉን እንዲወጣ ጠየቀ፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ተቆፍረው ክፍት በተተው ጉድጓዶች፣ በውሃ መውረጃ ቱቦዎች፣ በፍሳሽ…

ቱርክ በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው 104 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ውድመት ደርሶብኛል አለች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዚህ ዓመት በፈረንጆቹ የካቲት 6 ላይ በቱርክ በተከሰተው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 104 ቢሊየን ዶላር ገደማ ጉዳት መድረሱ ተነገረ፡፡ የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶኻን ÷ እንዲህ ያለው አደጋ በራስ ዐቅም ብቻ የሚመከት ባለመሆኑ…

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያለው እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያለው የሥራ እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን የአሜሪካ የውጭ ንግድ ጉዳይ ካውንስለሮች ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የውጭ ንግድ ጉዳይ ካውንስለሮች ቡድን በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለውን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።…

በዳዋ ዞን ከ121 ሺህ በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል ዳዋ ዞን ከ121 ሺህ በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል፡፡ በሶማሌ ክልል ባሉ 11 ዞኖች በተከሰተው ድርቅ 3 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ዜጎች ለተረጂነት ተጋልጠዋል። በዋናነት በክልሉ በድርቁ…