Fana: At a Speed of Life!

አቶ መላኩ አለበል እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ የቻይና ኢንዱስትሪዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዡዩአን በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ የቻይና ኢንዱስትሪዎችን ጎበኙ። ጉብኝቱ ኢንዱስትሪዎቹ እያጋጠሟቸው ያሉ ችግሮችን በአካል ተመልክቶ ማነቆዎችን ለመለየት ያለመ መሆኑ…

ሩሲያ የጥቁር ባህርን “የእህል ምርት መተላለፊያ” መስመር ዘጋች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ ዩክሬን የእህል ምርቷን በጥቁር ባህር ወደብ ወደ ዓለም ገበያ የምትልክበትን መስመር በድጋሚ መዝጋቷን አስታወቀች፡፡ ሞስኮ የእህል ማስተለላለፊያ መስመሩን በድጋሜ የዘጋጀው ዩክሬን “ለእልህ ምርት መተላለፊያ” የተፈቀደውን መስመር ለወታደራዊ…

አርሜኒያ እና አዘርባጃን በናጎርኖ ካራብክ አካባቢ ወታደራዊ ሀይል ላለመጠቀም ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አርሜኒያ እና አዘርባጃን የድንበር ግጭታቸውን ለመፍታት በናጎርኖ ካራብክ ተራሮች አካባቢ ላይ ወታደራዊ ሀይል ላለመጠቀም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ። የአዘርባጃኑ ፕሬዚዳንት ኢሃም አሊዬቭ እና የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሺንያን…

አሰሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የገዛ ቀጣሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረችውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የከተማዋ ፖሊስ አስታወቀ። ወንጀሉ የተፈጸመው ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 10:45 ሰዓት ሲሆን÷ ቦታው ደግሞ በአዲስ አበባ…

ስዊዲን በኢትዮጵያ ለሴቶች ሰላምና ደህንነት ግንባታ የ2 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስዊዲን በኢትዮጵያ ለሴቶች ሰላም እና ደህንነት ግንባታ የሚውል የ2 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ አድርጋለች፡፡ ድጋፉ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ሴቶች በተለያዩ ዘርፎች የሚኖራቸውን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚያስችል ተጠቁሟል፡፡ ድጋፉ የተባበሩት…

ለአፍሪካ ችግሮች እልባት ለመስጠት የወጣቶችን አቅም መጠቀም ያስፈልጋል- አቶ አደም ፋራህ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአፍሪካ ችግሮች እልባት ለመስጠት የወጣቶችን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ መጠቀም እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ፡፡ ብልጽግና ፓርቲ ከመላው አፍሪካ ለተወጣጡ የአፍሪካ ወጣት መሪዎች ጉባዔ ተሳታፊ ለሆኑ እንግዶች…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም የሚመለከታቸው ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ጥሪ አቀረቡ፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመ ልዩ አጣሪ ቋሚ ኮሚቴ የመተከል ግጭት መፍትሄና…

ከአላማጣ እስከ ቆቦ ያሉ አካባቢዎች ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል አገኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው የህወሓት ቡድን በከፈተው ጦርነት በደረሰ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ውድመት ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩት አላማጣ፣ ኮረም፣ ዋጃ፣ ጥሙጋ እና ቆቦ ከተሞች ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል አግኝተዋል፡፡ አገልግሎቱ እንደገና ለመመለስ በተደረገ ፈጣን…

በ50 ሚሊየን ዶላር እየተገነባ የሚገኘው የኢ-ኮሜርስ የጭነት አገልግሎት ማዕከል በቅርቡ ስራ እንደሚጀምር ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚሊየን ዶላር እያስገነባ ያለው ዘመናዊ የኢ-ኮሜርስ የጭነት አገልግሎት ማዕከል በቅርቡ ስራ እንደሚጀምር አስታወቀ። በዓለም የኢ-ኮሜርስ ንግድ እየተስፋፋ መሆኑን ተከትሎ አየር መንገዱ ተወዳዳሪነቱን ለማስቀጠል…

በኢትዮጵያ 3 ነጥብ 7 ሚሊየን አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም ማሳ እያለሙ ነው –  ኢንስቲትዩቱ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ 3 ነጥብ 7 ሚሊየን አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም ማሳ እያለሙ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ገለጸ፡፡ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሴ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በመኽር…