ኢትዮ – ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የማበረታቻ ሽልማት አበርክቷል።
በስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደው የሽልማት መርሐ ግብር ላይ አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች እንዳስመዘገቡት ውጤት ከአምስት ሺህ እስከ 300 ሺህ ብር የሚደርስ የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የኢትዮ - ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነችውና በ18ኛው የኦሪገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች…