Fana: At a Speed of Life!

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት 100 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ በደሴ ከተማ ያስገነባው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ነገ ይመረቃል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት 100 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ በደሴ ከተማ ያስገነባው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ነገ ይመረቃል። በ450 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ህንፃው ባለ 8 ወለል ሲሆን፥ ወቅቱ የደረሰበትን የሬዲዮ ስቱዲዮን ያካተተ…

ዩዌሪ ሙሴቪኒ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረውን ግጭት በሰላም ለመፍታት የወሰደውን እርምጃ እንደሚያደንቁ ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኡጋንዳውፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረውን ግጭት በሰላም ለመፍታት የወሰደውን እርምጃ እንደሚያደንቁ ገለፁ። አምባሳደር አለምፀሀይ መሰረት  ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ከኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኔ ጋር…

በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ የውጭ ሀገር ገንዘብ ተያዘ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሕብረተሰቡና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን የውጭ ሀገር ገንዘብ መያዙን ገለፀ፡፡ በተካሄደው ዘመቻ 27 ሺህ 491 የአሜሪካ ዶላር፣…

ኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚዋን ለማነቃቃት በዱባይ ቻምበርስ የልምድ ልውውጥ አድርጋለች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከመንግስት እና ከግሉ ዘርፍ የተወከሉ ልዑካን ቡድኗን ለልምድ ልውውጥ ወደ ዱባይ ኢሚሬትስ መላኳ ተገለጸ፡፡ ከኢትዮጵያ መንግስት ተልዕኮ ወስደው ወደ ዱባይ ያቀኑትን 10 ልዑካንን የመሩት የ”ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ኃላፊነቱ የተወሰነ…

በአሰቃቂ ሁኔታ ሰው የገደለው ግለሰብ በ21 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወንድሜን ገድሎብኛል በሚል ቂም በቀል በአሰቃቂ ሁኔታ ሰው የገደለው ግለሰብ በ21 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሽ ጎዳዳው መልኬ÷ ወንድሜን ገድሎብኛል በሚል ቂም በቀል አብዩ በሪሁንን ሚያዚያ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከምሽቱ5…

የደቡብ ሱዳንን የሽግግር ወቅት መራዘም በበጎ ጎን እንደሚመለከተው የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ሱዳንን የሽግግር ወቅት መራዘም የኢትዮጵያ መንግስት በበጎ ጎን እንሚቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ደቡብ ሱዳን የሽግግር ጊዜውን ለተጨማሪ 24 ወራት አራዝማለች። የውጭ…

1ሺህ 76 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1ሺህ 76 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ዛሬ በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ 1ሺህ 76 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው…

የተለያዩ ተቋማት የ4ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ አካል የሆነ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እንዲሁም ቱሪዝም ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አመራሮችና ሠራተኞች የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አከናውነዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴርና…