Fana: At a Speed of Life!

የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የ8 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የሚውል የ8 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡   ድጋፉን የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ደርቤ አስፋው ለሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ መሃመድ አስርክበዋል፡፡…

በምዕራብ ሸዋ ዞን በ33 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የውሃ ፕሮጀክት ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ አይደለም-ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በ33 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የውሃ ፕሮጀክት ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ አለመሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡   በዚህም የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በኑሯቸው ላይ ጫና እንዳሳደረባቸው ነው…

የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች በህዝብ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እቅድ አውጥተው እየሰሩ መሆኑን አስታወቁ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በህዝብ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የአጭር፣ የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜ እቅዶችን አውጥተው እየሰሩ መሆኑን የደቡብ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች አስታወቁ። የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ…

አቶ መላኩ ከጃፓን ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ኤጀንሲ አመራሮች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 17፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ከጃፓን ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ኤጀንሲ (ጃይካ) አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡   በውይይቱ የተለያዩ የስራ ሃላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን ÷ በተለይ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማሳደግ…

ከሳዑዲ ዓረቢያ 1ሺህ 254 ዜጎች ወደ አገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በተደረጉ ሦስት በረራዎች ከሳዑዲ ዓረቢያ 1ሺህ 254 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡   በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን የመመለሱ ጥረት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፥ በዛሬው ዕለት በተደረጉ…

ጀርመን በሩሲያ ነዳጅ ዘይት ላይ የተጣለውን ማዕቀብ እንድትቀበል የአውሮፓ ፓርላማ አባላት አሳሰቡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጀርመን  በሩሲያ  ነዳጅ ዘይት ላይ የተጣለውን ማእቀብ ማክበር ይኖርባታል ሲሉ የአውሮፓ ፓርላማ አባላት አሳሰቡ፡፡ በአውሮፓ ፓርላማ ከሁሉም የፖለቲካ ቡድኖች የተውጣጡ ሕግ አውጪዎች ቡድን ጀርመን በሩሲያ የኃይል ምንጮች ላይ እገዳ…

የወባ በሽታ ቁጥጥር ስራዎችን ለማጠናከር 20 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ አጎበር ለማሰራጨት ታቅዷል – ጤና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በመጪው ክረምት የወባ ትንኝ ቁጥጥር ስራዎችን ለማጠናከር 20 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ አጎበር እንዲሁም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ቤቶችን ለመርጨት መታቀዱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በዛሬው ዕለት…

ቻይና 4ኛውን ምዕራፍ ጨረቃን የማሰስ መርሃ ግብር በዚህ ዓመት እንደምትጀምር አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና አራተኛውን ምዕራፍ ጨረቃን የማሰስ መርሃ-ግብር በዚህ ዓመት ልትጀምር መሆኑን የቻይና ብሔራዊ የጠፈር አስተዳደር ምክትል ኃላፊ ው ያንሁዋ ተናገሩ። የአራተኛው ምዕራፍ ጨረቃን የማሰስ መርሃ-ግብር ዓላማም በደቡባዊ የጨረቃ ዋልታ ላይ ሣይንሳዊ…