Fana: At a Speed of Life!

አሸባሪዎቹ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የመንግሥትና የግል ተቋማትን ዘርፈዋል

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 6፣2014(ኤፍ ቢሲ) አሸባሪዎቹ ሕወሓትና ሸኔ ማኀበረሰቡ የሚገለገልባቸው በርካታ የመንግሥትና የግል ተቋማትን ዘርፈዋል፤ መውሰድ ያልቻሉትንም አውድመዋል ሲሉ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሀሰን ተናገሩ። አቶ…

“የኢትዮ-ፓኪስታን ሳይንትፊክ ዲፕሎማሲ ፎረም” ሊመሰረት ነው

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)"የኢትዮ-ፓኪስታን ሳይንትፊክ ዲፕሎማሲ ፎረም" ሊመሰረት መሆኑ ተገለፀ፡፡ ፎረሙ በሳይንቲፊክ ጉዳዮች ዙሪያ ኢትዮጵያና ፓኪስታን ያላቸውን ልምድ እንዲለዋወጡና በጋራ እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር…

89 ሺህ ዶላር የሚያወጡ 17 ቬንትሌተሮች ለጤና ሚኒስቴር ተበረከቱ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቦስተን ግብረ ሃይል ከቦስተን የኢትዮጵያውያን ስፖርት ክለብ ጋር በመተባበር 89 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ግምት ያላቸው 17 ቬንትሌተሮች ለጤና ሚኒስቴር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ክለቡ በአሜሪካ ለኢትዮጵያ ኢምባሲ ያስረከቧቸው ቬንትሌተሮች…

ላለፉት 27 አመታት በሶማሌ ክልል የደረሰው ችግርና ጭቆና ዳግም አይመለስም – አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የሶማሌ ክልል ተወላጅ የዳያስፖራ አባላት አገር ለማዳን በሚደረገው እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጎን መሆናቸውን ገለጹ። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የሶማሌ ክልል…

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች የ3 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሽብርተኛው የህወሓት ወራሪ ኃይል ለተፈናቀሉ የአፋር ክልል ወገኖች የሚውል የ3 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሽፈራው ተሊላ÷ በአፋርና አማራ ክልሎች በወራሪውና…

አሸባሪው ህወሓት ከኮምቦልቻ እስከ ሰመራ ባለው ማስተላለፊያ መስመር ላይ 52 ሚሊየን ብር የሚገመት ውደመት አድርሷል

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው ህወሓት ከኮምቦልቻ እስከ ሰመራ ባለው ማስተላለፊያ መስመር ላይ 52 ሚሊየን ብር የሚገመት ውደመት ማድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል አስታወቀ፡፡ የአሸባሪው ህወሃት ቡድን በአፋርና በአማራ ክልል በወረራ በያዛቸው አካባቢዎች…

በጅቡቲ እየተካሄደ ያለው ሄሪቴጅ ምክክር መድረክ ለአፍሪካ ቀንድ ትልቅ ጠቀሜታ ያለው ነው – አምባሳደር መሀሙድ ድሪር

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ5ኛው ጊዜ በጅቡቲ እየተካሄደ ያለው ሄሪቴጅ ምክክር መድረክ በአጠቃላይ ለአፍሪካ ቀንድ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አምባሳደር መሀሙድ ድሪር ገለጹ፡፡ ለ5ኛ ጊዜ በዓለም አቀፉ ሄሪቴጅ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት በጅቡቲ ሪፐብሊክ ርዕሰ መዲና ጅቡቲ…

ኢንጂነር ታከለ ኡማ በአፍዴራ የሚገኘውን የብሮሚን ማምረቻ ፋብሪካን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በአፍዴራ የሚገኘውን የብሮሚን ማምረቻ ፋብሪካን ጎበኙ። በጉብኝቱ ወቅት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ እና የፌደራል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ፋበሪካው አሁን ላይ ወደ…

ዶ/ር ታደሰ ካሳ የሚኒስትሮች ግብረ-ሃይል ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ተሸሙ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች የተፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር፣ ጥፋተኞችን በህግ ተጠያቂ ለማድረግና ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም የተመሰረተው የሚኒስትሮች ግብረ-ሃይል ዶ/ር ታደሰ ካሳን የግብረ-ሃይሉ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አድርጎ…

የመንግሥት ተቋማት የ100 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር የመንግሥት ተቋማትን የ100 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀመረ። በተመረጡ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ ጉብኝት ማካሄድ እና መረጃ በመሰብሰብ የተጀመረው ክትትልና ግምገማ፥ በዘርፍ አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች…