Fana: At a Speed of Life!

ኦስትሪያ ኮቪድ19 ማሻቀቡን ተከትሎ የእንቅስቅሴ ገደብ ጣለች

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኦስትሪያ እየጨመረ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመግታት በአገር አቀፍ ደረጃ የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሏን አስታወቀች። የእንቅስቃሴ ገደቡ ለ20 ቀናት የሚቆይ ሲሆን፥ ከ10 ቀናት በኋላ እንደገና እንደሚገመገም ተገልጿል።…

ጠ/ ሚ ዐቢይ ተደምረው ለእውነት ለቆሙ ኢትዮጵያውያን እና የአፍሪካ ቀንድ ዳያስፖራዎች አድናቆታቸውን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተደምረው ለእውነት ለቆሙ ኢትዮጵያውያን እና የአፍሪካ ቀንድ ዳያስፖራዎች አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጉዳዩን አስመልክተው በትዊተር ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷መደመር…

የሐረሪ ክልል የመንግስት ሰራተኞች የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚቃወመውን ንቅናቄ ተቀላቀሉ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል የመንግስት ሰራተኞች የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚቃወመውን ንቅናቄ ተቀላቀሉ፡፡ በመርሃ ግብሩ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላ፣ የብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮሮና ቫይረስ ክትባት ዘመቻ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮሮና ቫይረስ ክትባት ዘመቻ በአሶሳ ከተማ ተጀምሯል፡፡ ክትባቱ ለሚቀጥሉት አስር ቀናት 100 ሺህ ዜጎችን ተደራሽ ያደርጋል መባሉን የዘገበው ቤኒሻንጉል ጉሙዝ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ነው፡፡ አካባቢዎን ይጠብቁ!…

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ምስረታ ዛሬና ነገ ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አምስት ዞኖችና አንድ ልዩ ወረዳ በጋራ ሆነው የሚያቋቁሙት የደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ዛሬና ነገ በሚካሄዱ መርሀ ግብሮች 11ኛው ክልል ሆኖ በይፋ ይመሰረታል፡፡ የደቡብ ምዕራብ ህዝቦች መስከረም 20 ባካሄዱት ህዝበ ውሳኔ መሠረት…

ሀሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ የሚዲያ ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃው ተጠናክሮ ይቀጥላል – አቶ መሐመድ ኢድሪስ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ያስቀመጣቸውን ህገ-ደንቦችና የሙያውን ሥነ ምግባር በመጣስ ሀሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ የሚዲያ ተቋማት ላይ የሚወሰደው የእርምት እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አስታወቁ።…

ኢትዮጵያውያን በአንድ ቀን ብቻ በ27 አለማቀፍ ከተሞች ጣልቃ ገብነትን የሚቃወም ሰልፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13 ፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአለማቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያውያን በ27 ከተሞች የአሜሪካ መንግስት እና አንዳንድ የምእራባዊያንን መንግስታት በኢትዮጵያ ላይ እያደረጉ ያሉትን ጣልቃ ገብነትና ጫና የሚቃወም ሰልፍ አድርገዋል። ከደቡብ አፍሪካ እስከ ዋሽንግተን ዲሲ ነጩ…

ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የታወቁት የምዕራባውያን ሚዲያዎች በሱዳን መዶለታቸው ተሰማ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ላይ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የታወቁት የምዕራባውያን የሚዲያ ተቋማት ተወካዮች በካርቱም በሚደረግላቸው ድጋፍ በሱዳን ዋድ ሙዛሚል ከተማ መሰብሰባቸው ተገለጸ። በካርቱም መንግስት በሚደረግላቸው ድጋፍ በጋራ ሱዳን ዋድ…

መሰረታዊ ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአካባቢው ወጣቶች ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 12፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) መሰረታዊ ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአካባቢው ወጣቶች ተመርቀዋል። በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰጠኝ አወቀ ÷ የሀገር ደህንነት ጉዳይ የሁሉም በመሆኑ የተማረው…

ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድን ከስልጣን አንስቶ የሽግግር መንግሥት ለመመስረት የሚደረገውን ሙከራ እቃወማለሁ – ካረን ባስ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 12፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)በፖለቲካዊ ድርድርም ሆነ በወታደራዊ ኃይል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን ከስልጣን አንስቶ የሽግግር መንግሥት ለመመስረት የሚደረገውን ሙከራ እንደሚቃወሙ የአሜሪካ ኮንግረስ አባል ካረን ባስ ገለጹ፡፡ "በፖለቲካዊ ድርድር፣ አስፈላጊ ሆኖ…