Fana: At a Speed of Life!

በልማት ስራ ላይ የነበረንን ተሳትፎ በአዲሱ ዓመትም አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል- አቶ ሽመልስ አብዲሳ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በልማት ስራ ላይ የነበረንን ተሳትፎ በአዲሱ ዓመትም አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ አዲሱን ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡…

2 ሺህ 41 ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው እና ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶች እንዲወገዱ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ1 ሺህ 562 ድርጅቶች ምርቶች ላይ ባዕድ ነገሮች ተቀላቅለው በመገኘታቸው እንዲሁም የ479 ድርጅቶች ምርቶች ጊዜ ያለፈባቸው በመሆኑ እንዲወገዱ መደረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ የገበያና ፋብሪካ ኢንስፔክሽን ዳይሬክተር…

ጅማ የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክቶ ለ1 ሺህ 650 ዜጎች ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅማ የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክቶ ለ1 ሺህ 650 ዜጎች የበዓል መዋያ ስጦታ ተበርክቷል፡፡ የጅማ ከተማ አስተዳደር ከኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ምዕራብ ሪጅንና ፈያ ኢንተግሬትድ ጋር በመተባበር ነው ድጋፉን ያደረጉት። በዚህም…

አዲሱ ዓመት በተባበረ ክንድ የጠላትን ግብዓተ መሬት ፈጽመን የሠላም አየር የምንተነፍስበት ይሆናል-ኮ/ጀ/ደመላሽ ገ/ሚካኤል

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና ለመላው የፀጥታ አካላት ለ2014 ዓ.ም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። አዲሱ ዓመት ከውጪና ከውስጥ በአሸባሪው የህወሓት ጁንታ ቡድንና…

በአሸባሪው ህወሓት ወረራ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም ይሠራል – የሠላም ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ወረራ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም እንደሚሰራ የሠላም ሚኒስቴር አስታወቀ። የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በፈፀመው ወረራ የተፈናቀሉ ወገኖችን በቀጣይ በቋሚነት ማቋቋም በሚቻልበት…

አዲሱ ዓመት ኢትዮጵያ የድል ብስራት የምትሰማበት ዓመት ይሆናል- ትውልደ ኢትዮጵያውያን

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱ ዓመት ኢትዮጵያ የመከራ ጊዜዋን አልፋ የድል ብስራት የምትሰማበት ዓመት እንደሚሆን እምነታቸው መሆኑን በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ገለጹ። ኢትዮጵያ በ2013 ዓ.ም በችግርና በመከራ ውስጥ ያለፈችበት ፈታኝ ጊዜ…

ጠ/ሚ ዐቢይና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ለአቅመ ደካሞች የበዓል መዋያ ስጦታ አበረከቱ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚኖሩ አቅመ ደካሞች የበዓል መዋያ ስጦታ አበርክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩና ቀዳማዊት እመቤቷ…

በንጹኃን ዜጎች ላይ ጭፍጨፋ የሚፈጽመውን የሕወሃት አሸባሪ ቡድን ማጥፋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው-ሜ/ጀ እንዳልካቸው ወልደኪዳን

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በንጹሃን ዜጎች ላይ ጭፍጨፋ የሚፈጽመውን የሕወሃት አሸባሪ ቡድን ማጥፋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን የምድር ኃይል ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ገለጹ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዋሽ አርባ ውጊያ ቴክኒክ ትምህርት…

በሲዳማ ክልል ዋጋ የጨመሩና ምርት ያከማቹ ከ1ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሲዳማ ክልል የዘመን መለወጫ በዓል ገበያን በመጠቀም ተገቢ ያልሆነ ዋጋ የጨመሩና ምርት አላግባብ ያከማቹ ከ1 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች…

ከውጪ የገባው የምግብ ዘይት ለክልሎች እየተከፋፈለ ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘመን መለዋጫ በዓልን አስመልክቶ የዘይት አቅርቦት ችግር እንዳይከሰተ ከውጪ የገባው የምግብ ዘይት ወደ ክልሎች እየተከፋፈል መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሚኒስቴሩ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር…