Fana: At a Speed of Life!

የጳጉሜን መጨረሻ የድል ቃል ኪዳን ብስራት ቀን በደማቅ ሥነ ስርዓት ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ወጣቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት አዲስ አበባ ተከብሯል፡፡ በመርሐ ግብሩ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የማህበራዊ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር…

ፈተናዎች ሁሉ በድል ተጠናቀው ፊታችንን ወደ ልማት የምናዞርበት እሩቅ እይደለም- አቶ ደስታ ሌዳሞ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ አዲሱን ዓመት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ 2013 ዓ.ም 6ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ፍጹም ሠላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ…

የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ለህልውና ዘመቻው ለሦስተኛ ጊዜ የገንዘብና የዓይነት ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ለሶስተኛ ጊዜ ለህልውና ዘመቻ ለቆሙ ጀግኖች የሚውል በጥሬ ገንዘብ 12 ሚሊየን ብርና 102 ሰንጋዎች ድጋፍ አደረጉ። የዞኑ የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ምህረቱ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የዞኑ ህዝብ…

በህገ ወጥ መንገድ የኮቪድ -19  ህክምና አገልግሎት  የሰጠ ተጠርጣሪ  በቁጥጥር ስር  ዋለ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቦሌ ክፍለ ከተማ  በህገ ወጥ መንገድ የህክምና ፍቃድ ሳይኖረው የኮቪድ -19  ህክምና ማዕከል በመክፈት አገልግሎት እየሰጠ የነበረ ተጠርጣሪ  በቁጥጥር ስር  መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ። ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋለው በቦሌ…

የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል ያደረገ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንገኛለን – የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጊዜው የሚጠይቀውን ዘመናዊ የጉምሩክ አስተዳዳር ሥርዓት በመዘርጋት የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል ያደረገ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡ መረጃ እንደሚያሳየው ኮሚሽኑ በ2013 በጀት ዓመት ዓላማውን ለማሳካት…

በዩኔስኮ የተቋቋመው ዓለም አቅፍ ኮሚሽን የመጨረሻ ሪፖርቱን አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሚመራው እና በዓለም የትምህርት የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ ጥናት እንዲያደርግ በዩኔስኮ የተቋቋመው ዓለም አቀፍ ኮሚሽን የመጨረሻ ሪፖርቱን አጽድቋል። በፈረንጆቹ የፊታችን ጥቅምት ወር ለመንግሥታቱ ድርጅት…

ለኢትዮጵያ የገባነውን ቃል ኪዳን አድሰንና አክብረን፣ የኢትዮጵያን ድል እናበሥራለን-ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለኢትዮጵያ የገባነውን ቃል ኪዳን አድሰንና አክብረን፣ የኢትዮጵያን ድል እናበሥራለን አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸውላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ÷ድል የገቡትን ቃል በማክበር፣ለቃል ታምኖ በመሥራትና…

የንጋትን ጎህ ለማየት ድቅድቁን ጨለማ ማለፍ ግድ ነው-አቶ ደበሌ ቃበታ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ አዲሱን ዓመት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡   አቶ ደበሌ በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው የንጋትን ጎህ ለማየት ድቅድቁን ጨለማ ማለፍ ግድ ነው ብለዋል፡፡…

በጅማ ዞን ከ171 ሚሊ የን ብር በላይ ሲገነቡ የነበሩ የጤና ፕሮጀክቶች ተጠናቀቁ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በጅማ ዞን ከ171 ሚሊየን ብር በላይ ሲገነቡ የነበሩ የጤና ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸው ተገለፀ። በዞኑ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ ሲሆን÷ በተጠናቀቀው አመት 38 ፕሮጀክቶች ግንባታቸው መጠናቀቁ ነው…

የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች የአዲስ ዓመት የእርድ ቆዳን ለህልውና ዘመቻ ለመሰጠት ወሰኑ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች የአዲስ ዓመት የእርድ ቆዳን ለህልውና ዘመቻ ለመሰጠት ወሰኑ። የከተማ አስተዳደሩ ከቆዳና ሌጦ አቅራቢዎች ጋር ባዳረገው ውይይት በህልውና ዘመቻው እየተሳተፉ ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ድጋፍ እንዲሆን በዘመን መለወጫ ዕለት…