Fana: At a Speed of Life!

የ2014 የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 የውድድር ዘመን የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በዚህ መሰረት አርባ ምንጭ ከተማ ከመከላከያ፣ ባህር ዳር ከተማ ከአዲስ አበባ ከተማ ይጫወታሉ፡፡ በሌላ በኩል ፋሲል ከነማ ከሀዲያ…

በኢትዮጵያ የጡት ማጥባት ምጣኔው አበረታች ቢሆንም ሳይንሱ በሚያዘው መንገድ ማጥባት ላይ ክፍተት እንዳለ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጡት ማጥባት ሳምንት ከሐምሌ 25 እስከ ነሀሴ 1 "ጡት ማጥባትን መጠበቅ የጋራ ኃላፊነት ነው" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ነው። ይህንኑ አስመልክቶ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ መገለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው…

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በቶኪዮ ኦሊምፒክ በተገኙ ተጨማሪ ውጤቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በቶኪዮ ኦሊምፒክ በዛሬው እለት በተገኙ ተጨማሪ ውጤቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡ ፕሬዚዳንቷ “የኢትዮጵያ ልጆች አትሌት ለሜቻ ግርማ በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል የብር እንዲሁም በሴቶች…

የሱዳን ምሁራን የልዑካን ቡድን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 26፣ 2013 ( ኤፍ ቢ ሲ) የሱዳን ምሁራን የልዑካን ቡድን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ ውይይቱ በሱዳንና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ወቅታዊ ችግር ለመፍታትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን የበለጠ ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።…

የክተት ጥሪውን በመቀበል ወደግንባር ለማቅናት የወሰኑ ሰራተኞች ሸኝት ተደረገላቸው

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 26፣ 2013 ( ኤፍ ቢ ሲ)የሀገር አንድነትን አደጋ ላይ ለመጣል የሚሰራው ህገ-ወጥ ቡድን ላይ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በመደገፍ ለመዝመት የቆረጡ አራት የገቢዎች ሚኒስቴር ሰራተኞች በዛሬው ዕለት ሽኝት ተደረገላቸው፡፡ በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ “ሀገር እንዳትፈርስ ውድ…

በቶኪዮ ኦሊምፒክ በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ጉዳፍ ፀጋዬ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አስገኘች

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቶኪዮ ኦሊምፒክ በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ ጉዳፍ ፀጋዬ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አስገኘች፡፡ በውድድሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፋን ሃሰን ለኔዘርላንድስ የወርቅ ሜዳሊያ ስታስገኝ ኬንያዊቷ…

ከ165 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ ምርቶች ተያዙ

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 26፣ 2013 ( ኤፍ ቢ ሲ)ከ165 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የኮትሮባንድ እና በተለያዩ መጋዘኖች ተከማችቶ የተገኙ የተለያዩ ምርቶች መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡ ቢሮው የ2013 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም የቢሮው…

በቶኪዮ ኦሊምፒክ በወንዶች መሰናክል ለሜቻ ግርማ ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ አስገኘ

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 26፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በቶኪዮ ኦሊምፒክ ዛሬ 9፡15 በተካሄደው የወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ሩጫ ውድድር ለሜቻ ግርማ ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ አስገኝቷል፡፡ በዚህም ለሜቻ ግርማ  ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ  ሲያስገኝ  ጌትነት ዋለ ውድድሩን በአራተኝት…

የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በ2014 በጀት ዓመት እቅድ ስልጠናዊ ግምገማ በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በ2014 የበጀት ዓመት እቅድ ስልጠናዊ ግምገማ ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡   የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር…

በእነ ዶ/ር ደብረጺዮን የክስ መዝገብ ከተከሰሱ 62 ተከሳሾች መካከል 19ኙ ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ በጽሁፍ እንዲደርሳቸው ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በእነ ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የክስ መዝገብ ከተከሱ 62 ተከሳሾች መካከል 19ኙ ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ በጽሁፍ እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡   በዚህ መሰረትም አቶ ስብሐት ነጋ እና ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂምን ጨምሮ በሽብር…