Fana: At a Speed of Life!

የኮሚሽነሮች ዕጩ አቅራቢ ኮሚቴ ስራውን ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን በአዲስ መልክ ለማደራጀት በጸደቀው የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1224/2012 መሠረት የኮሚሽነሮች ዕጩ አቅራቢ ኮሚቴ ተሰብስቦ ስራውን ጀምሯል፡፡ በዚህ መሠረት…

ትናንት በተካሄዱ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 23 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ትናንት ምሽት በአውሮፓ የተለያዩ ከተሞች በተካሄዱ ውድድሮች ድል ቀንቷቸዋል። በዚህም በስፔን ማድሪድ በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር ያለምዘርፍ የኋላው በ31 ደቂቃ 17 ሰከንድ፣ በባርሴሎና በተካሄደ የ5…

ባንኩ ለ“ይቆጥቡ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” መርሃ ግብር ሽልማቶችን እጣ ለወጣላቸው እድለኞች አስረከበ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 23 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማህበር ለሁለተኛ ዙር ለ“ይቆጥቡ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” መርሃ ግብር ሽልማቶችን እጣ ለወጣላቸው እድለኞች አስረከበ። የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ተፈሪ መኮንን…

ፕሮፌሰር ሂሩት ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ  ኢትዮጵያን በመወከል  ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣…

በኦሮሚያ ክልል የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል መከሰቱን ኮሚሽኑ ገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተከሰተ የፀጥታ መደፍረስ የተሳተፉ ሰዎችና ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ ያደረሷቸው ጥቃቶች በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል…

የኢትዮጵያ የማዕድን ልማት ማዕከል ተቋቋመ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ‘የኢትዮጵያ የማዕድን ልማት ማዕከል' በሚል በማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስቴር ወጣኝነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢንጂነሪንግ ትምህርት ቤት መቋቋሙን የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አስታወቁ፡፡…

በደብረ ማርቆስ ከተማ በተከሰተ የእሳት አደጋ በ48 የንግድ ሱቆች ላይ ጉዳት ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተነሳ የእሳት አደጋ በ48 የንግድ ሱቆች ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አጃናው አዲስ  የእሳት አደጋው የደረሰው በጉልት ገበያ አዳራሽ መሆኑን…

በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ድንበር ሲያቋርጡ የነበሩ 11 ዜጎች ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ ድንበር በማቋረጥ ላይ የነበሩ 11 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሱን በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ፡፡ ኢትዮጵያውያኑ በህገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች…

የተማሪዎችን የፈጠራ ውጤቶች በአግባቡ መምራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ትምህርት ሚኒስቴር በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና፣ በጥበብና ሂሳብ ዘርፍ የሚቀርቡ የተማሪዎችን የፈጠራ ስራዎች ከዚህ በፊት ከነበረው አሰራር ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ረቂቅ መመሪያ ማዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡ መመሪያው ተወዳዳሪዎች…

ጠ/ሚ ዐቢይ የፈረንጆቹን አዲስ አመት አስመልክተው መልካም ምኞታቸውን ገለጹ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 23 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ለወዳጆቻችን እና ለአጋሮቻችን ሁሉ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ” ሲሉ መልዕክት አስተላለፉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት 2021 ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተስፋ እና ጥብዐት…