Fana: At a Speed of Life!

ሰሜን ምዕራብ ዕዝ ለውስብስብ ተልዕኮዎች የማይበገር ጠንካራ ዕዝ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰሜን ምዕራብ ዕዝ ግዳጅና ተልዕኮውን በጀግንነት እየፈፀመ የመጣ ዕዝ መሆኑን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ፡፡ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ባካሄደው የ2016 በጀት ዓመት የውይይት ማጠቃለያ ላይ…

ኮርፖሬሽኑ አዳዲስ ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ ከሚኒስቴሩ ጋር እንደሚሰራ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያለውን አዳዲስ የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በትብብር እንደሚሠራ ተገለጸ፡፡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሰሐ ይታገሱ (ዶ/ር) ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ…

የመዲናዋ አዲስ የከተማ ልማት ስትራቴጂ ዝግጅት በይፋ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የከተማ ልማት ስትራቴጂ ዝግጅት በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል፡፡ ስትራቴጂው የከተማዋን እምቅ አቅሞች በመለየት፣ እድሎችን በማንጠር፣ አዳጊ ፍላጎቶችን በማካተትና ተግዳሮቶችን በመቀነስ የረጅም ጊዜ ርዕይ…

ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት የሴፍትኔት ፕሮግራምን በሽግግር ራስን ለመቻል መጠቀም ይገባል- አምባሳደር ሽፈራው (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት የሴፍትኔት ፕሮግራምን በሽግግር ራስን ለመቻል መጠቀም እንደሚገባ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ገለጹ፡፡ በገጠር ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የተጋለጡ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ…

 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ለግማሽ ፍፃሜ አለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በካፍ የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የሴካፋ ሀገራት ማጣሪያ ውድድር እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ለግማሽ ፍፃሜ አለፈ፡፡ ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን…

የሕክምና ኮሌጁ የመካንነት ሕክምና አገልግሎትን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሥነ-ተዋልዶ ሕክምና ማዕከል የመካንነት ሕክምና አገልግሎቱን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የመካንነት ችግር ለመቅረፍ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ አምስት የሥነ-ተዋልዶ…

ኤምባሲው ለጠቅላይ ፍርድቤት ከ300 ሺህ ዶላር በላይ የሚገመት ድጋፍ አበረከተ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ300ሺህ ዶላር በላይ የሚገመት የስማርት ኮርት ሩም የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ድጋፍ አበረከተ፡፡ ኤምባሲው ድጋፉን ያደረገው በዓለም አቀፍ የናርኮቲክና ሕግ ማስከበር ጉዳዮች ቢሮ በኩል…

የፖክሮቭስክ ነዋሪዎች ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ ዩክሬን አዘዘች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ አጸፋዊ እርምጃ በመውሰድ ወደ ፖክሮቭስክ መገስገሷን ተከትሎ የከተማዋ ነዋሪዎች ቀያቸውን ለቀው እንዲወጡ ዩክሬን ማዘዟ ተሰምቷል፡፡ ዩክሬን ከሳምንታት በፊት ወደሩሲያ ግዛት ዘልቃ መግባቷ የሚታወስ ሲሆን ፥ ይህንንም የሁለቱ ሀገራት መንግስታት…

በመዲናዋ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት እና በአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ፡፡ ከችግኝ ተከላው በተጨማሪ የቤት እድሳት መርሐ-ግብር…