Fana: At a Speed of Life!

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ (ኤፍ ኤም ሲ) ሶላሪስ ሞተርስ  የተሰኘ በኤሌክትሪክ የሚንቀሳቀሱ ባለ 2 እና 3 እግር ተሽከርካሪዎች መገጣጠሚያ ፋብሪካ ዛሬ ተመርቋል፡፡ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጎልባ ቀበሌ የተገነባው ፋብሪካው በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ…

የቀድሞ የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ  የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ሳም ኑጆማ በ95 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት መለያታቸውን የወቅቱ ፕሬዚዳንት ናንጎሎ ሙቡምባ አስታውቀዋል፡፡ ናሚቢያ በፈረንጆቹ 1990 ነጻነቷን ካወጀች በኋላ የሀገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት የነበሩት ሳም…

ብሔራዊ መግባባትን ለማጎልበት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ (ኤፍ ኤም ሲ) ብሔራዊ መግባባትን ለማጎልበት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ሁለተኛው መደበኛ ጉባኤ በተለያዩ መስኮች…

ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው ዕድገት እያስመዘገበች ነው – የአይ ኤም ኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በግብርና፣ በአገልግሎት እና በሌሎች ዘርፎች ቀጣይነት ያለው ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ገለፁ። የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ማኔጂንግ…

አገልግሎቱ ቀልጣፋ የትራንስፖር አገልግሎት ለመስጠት ተቋማዊ ማሻሻያ ማድረጉን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ የአውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልገሎት መስጠት የሚያስችል ተቋማዊ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ የአውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት የተቋሙን አዲስ መለያ እና የስፖርት ትጥቅ…

ሩሲያና ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ተስማሙ። የሩሲያ ጤና ሚኒስትር ሚካየል ሙራሽኮ እና በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ውይይት አካሄደዋል። በውይይታቸው ሁለቱ ሀገራት የህክምና ትምህርትን እና…

ከኢትዮጵያ የንግዱ ዘርፍ አመራሮችና ስራ ፈጣሪዎች ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል- የአይ ኤም ኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከኢትዮጵያ የንግዱ ዘርፍ አመራሮችና ስራ ፈጣሪዎች ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ ገለጹ፡፡ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢንቨስትመንቱ ዘርፍ መሻሻል…

በእንጅባራ ከአንዲት እናት 24 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ በቀዶ ሕክምና ተወገደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ከአንዲት እናት 24 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ በቀዶ ሕክምና መወገዱ ተገልጿል፡፡ የ38 ዓመት ታካሚዋ ወ/ሮ ትሁን ገነቱ በፓዌ ልዩ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ÷ሁለት ሰዓት አካባቢ የወሰደ የተሳካ ከባድ ቀዶ ሕክምና አድርገው…

የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ እንዲያገኙ የታየው ቁርጠኝነት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት መሪዎች የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ እንዲያገኙ ያሳዩት ቁርጠኝነትና አጋርነት ለሌሎች ምሳሌ እንደሚሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ እና የደቡባዊ አፍሪካ የልማት…

አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው የግማሽ ማራቶን አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዱባይ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ያለምዘርፍ 1 ስዓት ከ7ደቂቃ ከ09 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በአንደኝነት ማጠናቀቋን የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል።