Fana: At a Speed of Life!

በጎንደር ከተማ በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ነገ ይመረቃሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወጪ የተደረገባቸው 67 ፕሮጀክቶች ነገ እንደሚመረቁ የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ገለጹ፡፡ ፕሮጀክቶቹ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተቱ የቆዩ መሆናቸውን አቶ ቻላቸው…

የአፍ ውስጥና የፊት ቀዶ ሕክምና ዘርፍን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍ ውስጥ፣ የመንጋጋና የፊት ቀዶ ሕክምና ዘርፍን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የአፍሪካ የአፍ ውስጥ፣ የመንጋጋና የፊት ቀዶ ሕክምና ሐኪሞች ማህበር ኮንፈርንስ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የአፍ…

ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) የጣሊያን ድርጅቶች በጸሀይ ሀይል ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሰማሩ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) የጣሊያን ድርጅቶች በጸሀይ ሀይል ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሰማሩ ጥሪ አቀረቡ። ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር አዉጉስቲኖ ፓሊሲ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም የጣሊያን ድርጅቶች…

ሊዮኔል ሜሲ በዓለም አቀፍ ጨዋታዎች የግብ እድሎችን አመቻችቶ የማቀብል ክብረወሰንን ተጋራ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አርጅንቲናዊው አጥቂ ሊዮኔል ሜሲ በዓለም አቀፍ ጨዋታዎች 58 የግብ እድሎችን አመቻችቶ የማቀብል ክብረወሰንን ከቀድሞው አሜሪካዊ አጥቂ ላንደን ዶንቫን ጋር ተጋርቷል፡፡ ሜሲ ትላንት ምሽት በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አርጀንቲና ፔሩን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት…

በማንቼስተር ከተማ ኤአይ ካሜራ ለትራፊክ ቁጥጥር አገልግሎት እየዋለ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ማንቼስተር ከተማ የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ (ኤአይ) ካሜራ ለትራፊክ ቁጥጥር አገልግሎት እየዋለ መሆኑ ተነገረ። በከተማዋ 3 ሺህ 200 ሹፌሮች በማሽከርከር ላይ ሳሉ ስልክ ሲያወሩ እና ቀበቶ ሳያስሩ ሲንቀሳቀሱ በኤአይ ካሜራዎች ተይዘዋል።…

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በብቃት ላይ የተመሠረተ አመራር እንዲኖር እየተሰራ ነው – ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በብቃት ላይ የተመሠረተ አመራር እንዲኖር እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አስታወቁ፡፡ ትምህርት ሚኒስቴርና የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ…

ካናቢስ የተሰኘውን የተከለከለ አደንዛዥ ዕጽ ሲያመርት የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ማያ ከተማ ሀረማያ ክፍለ ከተማ በአቋራጭ መበልጸግን በማሰብ ካናቢስ የተሰኘውን የተከለከለ አደንዛዥ ዕጽ ሲያመርት የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የከተማው ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው ጥቆማ መሰረት አቶ…

ከአሰሪዎቿ 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረትና ገንዘብ የሰረቀችው የቤት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአሰሪዎቿ 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረትና ገንዘብ የሰረቀችው የቤት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር መዋሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ ወንጀሉ የተፈፀመው ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ስሙ አያት ዞን…

በኦሮሚያ ክልል የሩዝ ሰብል ምርት መሰብሰብ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ2016/17 የምርት ዘመን በመኸር ወቅት የለማ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በላይ የሩዝ ሰብል ምርት መሰብሰብ ጀመረ፡፡ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ ተገኝተው የሩዝ ምርት…

ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ13 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አምረፍ ሄልዝ አፍሪካ የተባለው ድርጅት ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከ13 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡ የጤና ስራ ለመደገፍ የሕክምና ቁሳቁስ በበቂ ሁኔታ እንደሚያስፈልግም የክልሉ ጤና ቢሮ ገልጿል፡፡…