Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የፈረንሳይ ከዋክብት የጎል ድርቅ በአውሮፓ ዋንጫ አዲስ ታሪክ ሆኖ ተመዝግቧል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የላቀ ክህሎት ያላቸው ከዋክብትን የያዘው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ በክፍት ጨዋታ አንድም ግብ ሳያስቆጥር ግማሽ ፍጻሜን በመቀላቀል አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል፡፡ ትናንት ምሽት ከ120 ደቂቃ ፍልሚያ በኋላ ፈረንሳይ ፖርቹጋልን በመለያ ምት 5 ለ 3 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፏ ይታወሳል። የትናንት ምሽቱ ውጤት ለፈረንሳይ በድል አድራጊነት ይመዝገብ እንጂ ሀገሪቱ በአውሮፓ ዋንጫ ታሪክ የራሷ ተጫዋቾች ከክፍት ጨዋታ ግብ ሳያስቆጥሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ያለፈች የመጀመሪያዋ…
Read More...

በአውሮፓ ዋንጫ እንግሊዝ ከስዊዘርላንድ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር እንግሊዝና ስዊዘርላንድ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡ የ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል። በዚህም መሰረት እንግሊዝ ከስዊዘርላንድ ምሽት 1:00 ላይ በዱሴልዶርፍ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ በጥሎ…

ወልቂጤ ከተማ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት ወልቂጤ ከተማ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9:00 ላይ በተካሄደ የሊጉ ጨዋታ አዳነ በላይነህ ባስቆጠራት ግብ ወልቂጤ ከተማ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

በፓሪስ ኦሊምፒክ ውድድሮች ኢትዮጵያን የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ውድድሮች በአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው መለየታቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በዚህም ፡- 800 ሜትር ሴቶች አትሌት ፅጌ ድጉማ፣አትሌት ሐብታም ዓለሙ፣አትሌት ወርቅነሽ መለሰ፣አትሌት ንግስት ጌታቸው (ተጠባባቂ) 1ሺህ…

የቱርኩ የመሐል ተከላካይ ዴሚራል የሁለት ጨዋታ እገዳ ተጣለበት

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቱርኩ የመሐል ተከላካይ ሜሪህ ዴሚራል ሀገሩ ቱርክ ከኦስትሪያ ጋር በነበረው ጨዋታ ግብ ካስቆጠረ በኋላ ባሳየው አወዛጋቢ የደስታ አገላለፅ ምልክት በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ሁለት ጨዋታ እንዲታገድ ተደርጓል፡፡ የ26 ዓመቱ ዴሚራል በአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ኦስትሪያ ላይ ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን ለመግለፅ…

በአውሮፓ ዋንጫ ጀርመንና ስፔን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር አዘጋጇ ጀርመን ከስፔን ጋር የምታደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡ የ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡ በዚህ መሰረትም አዘጋጇ ጀርመን እና ስፔን ምሽት 1 ሰዓት ላይ በስቱትጋርት አሬና ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ…

ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ። ዛሬ 9:00 ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ አማኑኤል ኤርቦ (ሁለት)፣ ዳዊት ተፈራ እና ተገኑ ተሾመ ባስቆጠሯቸው ግቦች አሸንፎ ወጥቷል። በተመሳሳይ በፕሪሚየር ሊጉ ምሽት ላይ በተካሄደ…