ስፓርት
አዳማ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ 0 ለ 0 ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ ነው የተጠናቀቀው።
እንዲሁም በአዲስ አበባ ስታዲያም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተጀመረው የአርባ ምንጭ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ጨዋታ በፋሲል ከተማ 2 ለ 1 መሪነት የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቀዋል።
የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም…
Read More...
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል።
ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ግቦች እንዳልካቸው ጥበቡ እና ቃለአብ ውብሸት (በራሱ ላይ) አስቆጥረዋል።
በጨዋታው ሀዲያ ሆሳዕናን…
የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ባካሪ ሳኛ በአዲስ አበባ..
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የአርሰናል እና የማንቸስተር ሲቲ የቀድሞ ተጫዋች ባካሪ ሳኛ አዲስ አበባ ይገኛል፡፡
አንጋፋው ተጫዋች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከማክሮን የትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር የሚያደርገው የሁለትዮሽ ስምምነት አካል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ ተመልክቻለሁ ያለው ሳኛ÷…
አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወትና አትሌት ቢቂሌ አንበሴ የ10 ኪ.ሜ የጐዳና ውድድርን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት እና አትሌት ቢቂሌ አንበሴ የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጐዳና ውድድርን አሸንፈዋል።
ዛሬ ማለዳ በሐዋሳ ከተማ በተደረገው የ10 ኪሎ ሜትር የጐዳና ውድድር በወንዶች አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት በቀዳሚነት አጠናቅቋል።
አትሌት ሀጎስ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 28 ደቂቃ 2 ሰከንድ ከ94 ማይክሮ…
አርሰናል ከማንቼስተር ዩናይትድ የሚያደርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀጥሎ ሲካሄድ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በኢምሬትስ ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡
በሊጉ ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው የሚኬል አርቴታ ቡድን አርሰናል ወደ አሸናፊነት ለመመለስና መሪነቱን ለማጠናከር…
ማንቼስተር ሲቲ ወልቭስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ወልቭስን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የማንቼስተር ሲቲን ግቦች ኦማር ማርሙሽ እና አንቶኒዮ ሴሜኒዮ አስቆጥረዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን ወደ 46 ከፍ በማድረግ የሊጉ መሪ አርሰናል ነገ ጨዋታውን እስከሚያደርግ ያለውን የነጥብ…
አርሰናል ከማንቼስተር ዩናይትድ – ተጠባቂው ፍልሚያ
አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች ይጀምራል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ በውድድር ዓመቱ እስካሁን አንድ ጨዋታ ብቻ ካሸነፈው ወልቭስ ጋር ይጫወታል፡፡
በሊጉ ካደረጋቸው ያለፉት አራት ጨዋታዎች በአንዱም ማሸነፍ ያልቻለው ማንቼስተር ሲቲ ወደ ድል…