ስፓርት
ሀዋሳ ከተማ እና መቻል አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ9ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ እና መቻል 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኮሊንስ ኮፊ መቻልን መሪ ማድረግ የቻለ ሲሆን፥ የሀዋሳ ከተማን የአቻነት ግብ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ሀድያ ሆሳዕና ከነገሌ አርሲ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ሲሆን፥ አርባ ምንጭ ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ይጫወታሉ፡፡
ቀን 10 ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ ከፋሲል…
Read More...
አርሰናል በአስቶን ቪላ ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ15ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አስቶን ቪላ አርሰናልን 2 ለ 1 አሸንፏል።
በሜዳው የሊጉን መሪ አርሰናልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ማቲ ካሽ እና ኢሚሊያኖ ቡዌንዲያ ስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።
የአርሰናልን ብቸኛ ግብ ሊያንድሮ ትሮሳርድ አስቆጥሯል።
የ15ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ15ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ቀን 9 ሰዓት 30 ላይ የሊጉ መሪ አርሰናል ወደ ቪላ ፓርክ በማቅናት ከአስቶንቪላ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት መድፈኞቹ በሊጉ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሦስቱን አሸንፈው…
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የፊፋ የሰላም ሽልማትን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) የሰላም ሽልማትን አሸንፈዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሽልማቱ የተበረከተላቸው በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ባለው የ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ የዕጣ ማውጣት ሥነ ስርዓት ላይ ነው፡፡
በዚህ ወቅትም ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከፊፋው ፕሬዚዳንት ጂያን…
በደከመው ሊቨርፑል ተሽሎ የተገኘው ሶቦዝላይ …
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በውድድር ዓመቱ ደካማ እንቅስቃሴ እያሳየ በሚገኘው ሊቨርፑል በግሉ የተሻለ ብቃት በማሳየት እያንጸባረቀ የሚገኘው ዶሚኒክ ሶቦዝላይ፡፡
በአሰልጣኝ አርኔ ስሎት የሚመራው የመርሲሳይዱ ክለብ በሁሉም ውድድሮች አስቸጋሪ ጊዜ እያሳለፈ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ሊቨርፑል ወጥ ብቃት ማሳየት ተስኖት ፈታኝ የውድድር ዓመት እያሳለፈ…
ማንቼስተር ዩናይትድ ደረጃውን ለማሻሻል የሚያደርገው ጨዋታ…
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ ዛሬ ምሽት ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይገናኛል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ ዌስትሃምን በሚያስተናግድበት ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ ነጥቡን 24 በማድረስ 5ኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች በፕሪሚየር ሊጉ…
አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር ዛሬ ምሽት ከብሬንትፎርድ ጋር ይጫወታል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል የሊጉን መሪነት ለማጠናከር ዛሬ ምሽት ብሬንትፎርድን በሜዳው ያስተናግዳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ትናንት ምሽት ፉልሃምን 5 ለ 4 ማሸነፉን ተከትሎ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡
መድፈኞቹ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያላቸውን…