ስፓርት
ሊቨርፑል ፍሎሪያን ቪርትስን ከባየር ሊቨርኩሰን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል ጀርመናዊውን የአጥቂ አማካይ ፍሎሪያን ቪርትስ የክለቡ የዝውውር ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ከባየር ሊቨርኩሰን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
ሊቨርፑል ለተጫዋቹ ዝውውር 100 ሚሊየን ፓውንድ እና ተጨማሪ 16 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍል ሲሆን፥ ለአምስት አመት በአንፊልድ የሚያቆየውን ውል ፈርሟል።
ፍሎሪያን ቪርትስ ለቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሊቨርኩሰን 197 ጨዋታዎችን በማድረግ 57 ግቦችን አስቆጥሯል።
የ22 አመቱ ቪርትስ ለቀዮቹ ፊርማውን ካኖረ በኋላ በሰጠው አስተያየት፥ ለረዥም ጊዜ…
Read More...
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመኑ ምርጥ ተጫዋች የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመኑ ምርጥ ተጫዋች የመጨረሻ ስድስት ዕጩዎች ዝርዝር ይፋ ሆኗል፡፡
በሊጉ 15ኛ ደረጃን በመጨረስ አስከፊ የውድድር አመትን ያሳለፈው የማንቼስተር ዩናይትድ አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴስ ከእጩዎቹ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል።
ብሩኖ ለቀያይ ሰይጣኖቹ ስምንት…
የክለቦች ዓለም ዋንጫ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሳታፊ ክለቦችን ቁጥር ወደ 32 ከፍ በማድረግ ባሳለፍነው ቅዳሜ ምሽት የተጀመረው የፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ተጠናቅቀዋል፡፡
በስምንቱ ምድቦች በተደረጉ 16 ጨዋታዎች በድምሩ 44 ግቦች ሲቆጠሩ፥ 6ቱ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተቋጭተዋል፡፡ በእነዚህ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዎች 5 ቀይ ካርዶች…
ሚካዬሎ ሙድሪክ አበረታች ንጥረ ነገር በመጠቀም ክስ ተመሰረተበት
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዩክሬናዊው የቼልሲ ክንፍ ተጫዋች ሚካዬሎ ሙድሪክ ያልተፈቀደ አበረታች ንጥረ ነገር በመጠቀም በእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር ክስ ቀርቦበታል፡፡
የ24 ዓመቱ ተጫዋች ከአበረታች ንጥረ ነገር ጋር ተያይዞ ካሳለፍነው ታሕሳስ ወር ጀምሮ ከእግር ኳስ ውድድሮች መታገዱ ይታወሳል፡፡
አሁን ላይም ሙድሪክ ያልተፈቀደ…
ማንቼስተር ዩናይትድ ከአርሰናል በመጀመሪያው ሳምንት ይገናኛሉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት የጨዋታ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል።
በዚሁ መሰረት ማንቼስተር ዩናይትድን ከአርሰናል በመጀመሪያው ሳምንት የሚያገናኘው መርሐ ግብር ከወዲሁ ተጠባቂ ሆኗል።
ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል በመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ቦርንማውዝን በአንፊልድ ያስተናግዳል።
በሌሎች…
ድሬዳዋ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ መቆየቱን አረጋገጠ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ስሑል ሽረን በማሸነፍ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በወንጂ ሁለገብ ስታዲየም ከሊጉ መውረዱን ያረጋገጠውን ስሑል ሽረን የገጠመው ድሬዳዋ ከተማ 4 ለ 2 አሸንፏል፡፡
የድሬዳዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች መስዑድ መሐመድ (2) እንዲሁም ዮሀንስ ደረጀ…
ሲዳማ ቡና እና አርባ ምንጭ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና አርባ ምንጭ ከተማ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ረፋድ 3፡30 ላይ በወንጂ ሁለገብ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ነው ሁለቱ ቡድኖች 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት የተለያዩት።
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ቀን 9 ሰዓት ባህር ዳር ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ…