ስፓርት
የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሳዳት ጀማል ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሳዳት ጀማል ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡
ሳዳት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በተለያዩ ክለቦች በግብ ጠባቂነት ተጫውቶ ያሳለፈ ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ በመሆን አገልግሏል፡፡
የቀድሞ ተጫዋችና አሰልጣኝ ሳዳት ጀማል በገጠመው ህመም የህክምና ርዳታ ሲደረግለት ቆይቶ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሳዳት ጀማል ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ፣ ለወዳጅ…
Read More...
ሪያል ማድሪድ ካይራት አልማቲን 5 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ የካዛኪስታኑን ክለብ ካይራት አልማቲን 5 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ45 በተደረገው ጨዋታ ፈረንሳዊው አጥቂ ኬሊያን ምባፔ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሲሰራ÷ ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና በራሂም ዲያዝ አስቆጥረዋል፡፡
በሌላ ጨዋታ…
ዊሊያም ሳሊባ በአርሰናል ውሉን አራዘመ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ በአርሰናል ለተጨማሪ አምስት አመታት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡
ሪያል ማድሪድ የ24 ዓመቱን ተጫዋች ለማስፈረም ጥብቅ ፍላጎት እንዳለው ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
ሆኖም ተጫዋቹ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በኢምሬትስ ለመቆየት የተስማማ ሲሆን፥ በመጪው ክረምት የሚያበቃውን ውሉን አድሷል፡፡…
ጆዜ ሞሪንሆን ከቀድሞ ክለባቸው ቼልሲ የሚያገናኘው የዛሬ ምሽት ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ2ኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች ይደረጋሉ፡፡
ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ቤኔፊካን እየመሩ በስታምፎርድ ብሪጅ የቀድሞ ክለባቸው ቼልሲን የሚገጥሙበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ፖርቹጋላዊ አሰልጣኝ ከምሽቱ ጨዋታ አስቀድሞ ስለ ቀድሞ ክለባቸው በሰጡት…
የኢትዮጵያ ዋንጫ የሚጀምርበት ቀን ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የ2018 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ የሚጀመርበትን ቀን ይፋ አድርጓል።
ፌደሬሽኑ እንደገለጸው ÷ የዘንደሮው የኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታ በመጪው ጥቅምት 9 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ይጀመራል፡፡
በዚህ መሰረትም የኢትዮጵያ ዋንጫ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ከጥቅምት 9 እስከ 11 ቀን 2018…
አስቶንቪላ ፉልሃምን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶንቪላ ፉልሃምን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ፉልሀም በራውል ሄሚኔዝ ግብ ቀዳሚ ቢሆንም ባለሜዳው አስቶንቪላ ዋትኪንስ፣ ማክጊን እና ቡዌንዲያ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
የሊጉ መርሃ ግብር…
ኒውካስል ዩናይትድ ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አርሰናል ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
በ6ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ዛሬ መድፈኞቹ ምሽት 12፡30 ላይ ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር ከባድ ፍልሚያ ያደርጋሉ።
የሊጉ መሪ የሆነው ሊቨርፑል በትናንትናው ዕለት ሽንፈት ማስተናገዱን ተከትሎ አርሰናል በመካከላቸው…