ስፓርት
ማንቼስተር ዩናይትድ ሌስተር ሲቲን 3 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በተመሳሳይ 11 ሠዓት ላይ ሦስት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡
በዚሁ መሠረት በሜዳው ሌስተር ሲቲን ያስተናገደው ማንቼስተር ዩናይትድ 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በሌላ በኩል ቶተንሃም ሆትስፐር በኢፕስዊች ታውን 2 ለ 1 እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት በኒውካስል ዩናይትድ 3 ለ1 ተሸንፈዋል፡፡
Read More...
ማንቼስተር ሲቲ በብራይተን ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በብራይተን ተሸንፏል፡፡
ምሽት 2፡30 በተደረገው ጨዋታ ብራይተን ማንቼስተር ሲቲን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የብራይተንን ግቦች ዣኦ ፔድሮ እና ማት ኦሪሊይ ሲያስቆጥሩ የማንቼስተር ሲቲን ብቸኛ ግብ ደግሞ ኧርሊንግ ሃላንድ…
ዎልቭስ፣ ብሬንት ፎርድና ፉልሃም ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በተደረጉ የ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዎልቭስ፣ ብሬንት ፎርድና ፉልሃም ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋ፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረጉ 4 ጨዋታዎች ዎልቭስ ሳውዝ ሃፕተንን፣ ፉልሃም ክሪስታል ፓላስን በተመሳሳይ 2 ለ 0 ሲያሸንፉ ብሬንትፎርድ ደግሞ ቦርንማውዝን 3 ለ 2 ረትቷል፡፡…
ዋሊያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ከሁለት ሳምንት በኋላ ያደርጋሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንበ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ አምስተኛ እና ሥድስተኛ የምድብ ጨዋታዎቹን ያደርጋል፡፡
በወጣው መርሐ-ግብር መሠረትም ዋሊያዎቹ ሕዳር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከታንዛኒያ አቻቸው ጋር እንደሚጫወቱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
እንዲሁም ሕዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከዲሞክራቲክ…
ሀድያ ሆሳዕና ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ7ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የሀድያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ጎልም ሰመረ ሃፍተይ በ48ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡
እንዲሁም ምሽት 1 ሠዓት ላይ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይጫወታሉ፡፡
እንዲሁም ምሽት 1 ሠዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ…
የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ቀጥለው ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ አራተኛ ዙር ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ።
ምሽት 2 ሠዓት ከ45 ላይ የቤልጂየሙ ክለብ ብሩጅ ከእንግሊዙ አስቶንቪላ፤ እንዲሁም የዩክሬኑ ሻካታር ዶኔስክ ከስዊዘርላንዱ ያንግ ቦይስ ጋር ይጫወታሉ፡፡
በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር ምሽት 5 ሠዓት ሳንሲሮ ጁሴፔ ሜዛ ላይ ኢንተር…
የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይቀጥላሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ አራተኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ሲካሄዱ ሪያል ማድሪድ ከኤሲሚላን እና ሊቨርፑል ከባየርሊቨርኩሰን የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 2 ሠዓት ከ45 ላይ የሆላንዱ ፒኤስቪ ከስፔኑ ዢሮና እንዲሁም የስሎቫኪያው ስሎቫን ብራቲስላቫ ከክሮሺያው ዳይናሞ ዛግሬብ ይጫወታሉ፡፡
በሌላ የጨዋታ…