ስፓርት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛው ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም 3:30 ላይ በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሳይመን ፒተር ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ሦስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 9 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከባሕር ዳር ከተማ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ከተማ ከወላይታ ድቻ ይገናኛሉ።
በሌላ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ያሸነፈ…
Read More...
5ኛው ስፖርት ለልማትና ለሠላም ቀን እየተከበረ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 5ኛው ሀገር አቀፍ ስፖርት ለልማት እና ለሠላም ቀን በኦሮሚያ ክልል ደምቢዶሎ ከተማ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር የሚከበረው ቀኑ፤ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና በፓናል ውይይት እየተከበረ መሆኑ ተገልጿል።
በፓናል ውይይቱ ላይ…
አትሌት በዳቱ ሂርጳ በፓሪስ ማራቶን አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ በተካሄደው የፓሪስ ማራቶን በሴቶች ኢትዮጵያውያኑ በዳቱ ሂርጳ እና ደራ ዲዳ ተከታትለው በመግባት በበላይነት አጠናቅቀዋል፡፡
አትሌት በዳቱ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ45 ሰከንድ እንዲሁም ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ ሰዓት 1ኛ እና 2ኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል፡፡
የወንዶቹን ውድድር ኬንያዊው…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 4 ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ 4 ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ይበልጥ እየቀረበ ያለው ሊቨርፑል ቀን 10 ሰዓት ዌስትሃምን በአንፊልድ የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል።
ሊቨርፑል የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ ከቀሩት ሰባት ጨዋታዎች 9 ነጥብ ማግኘት ከቻለ የሌሎች ክለቦችን ውጤት…
አርሰናል እና ብሬንትፎርድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል እና ብሬንትፎርድ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
ምሽት 1፡30 ላይ በሜዳቸውና እና በደጋፊያቸው ፊት ብሬንትፎርንድን ያስተናገዱት መድፈኞቹ በድጋሚ ነጥብ ጥለዋል፡፡
አርሰናል በ61ኛው ደቂቃ ላይ ቶማስ ፓርቴ ባስቆጠረው ግብ መምራት ችሎ የነበረ ቢሆንም ዮአን…
ማንቼስተር ሲቲ ከመመራት ተነስቶ ክሪስታል ፓላስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ 32ኛ ሳምንት ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከመመራት ተነስቶ ክሪስታል ፓላስን 5 ለ 2 አሸንፏል፡፡
በምሳ ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ክሬስታል ፓላስ በኤዜ እና ሪቻርድስ ግቦች 2 ለ 0 መምራት ቢችልም ኬቨን ዴብሮይን እና ኦማር ማርሙሽ አከታትለው ባስቆጠሯቸው ግቦች በ2 አቻ ውጤት ወደ እረፍት…
የኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአለም ሻምፒዮና ማጣሪያ በስፔን ይደረጋል-ኮማንደር ስለሺ ስህን
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ10 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያን በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመወከል በስፔን ማላጋ የማጣሪያ ውድድር እንደሚደረግ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡
የፌዴሬሽኑፕሬዚዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ ከ10 ሺህ ሜትር ውጪ ባሉ ርቀቶች አትሌቶች በሀገር ውስጥ በሚደረገው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና…