ስፓርት
የኢትዮጵያ አዳጊዎች ኦሊምፒክ በጥቅምት ወር ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሁለተኛው የኢትዮጵያ አዳጊዎች ኦሊምፒክ ጨዋታ በመጪው ጥቅምት ወር በአዲስ አበባ ይደረጋል አለ፡፡
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በሰጡት መግለጫ÷ በውድድሩ እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ አዳጊዎች ይሳተፋሉ፡፡
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ በአዳጊ ስፖርተኞች መካከል የኦሊምፒክ መንፈስን በማስረፅ ተሳትፏቸውን ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል።
በኦሊምፒክ ጨዋታው የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ስፖርተኞች በአንጎላ በሚካሄደው…
Read More...
ለኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ የቡድን አባላት ሽልማት ተበረከተ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ የቡድን አባላት የእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
ክለቡ በአጠቃላይ ከ25 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን እንዲያሳካ ላስቻሉት ሁሉም የቡድኑ አባላት ሽልማት ማበርከቱን የክለቡ ፕሬዚዳንት ምንተስኖት ደሳለኝ ለፋና…
ማዱኬ ባጋጠመው ጉዳት ለሁለት ወራት ከሜዳ ይርቃል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርሰናል የፊት መስመር ተጫዋች ኖኒ ማዱኬ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ለሁለት ወራት ያህል ከሜዳ እንደሚርቅ ተነግሯል፡፡
ተጫዋቹ ባሳለፍነው እሑድ አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ አንድ አቻ በተለያዩበት የሊጉ የ5ኛ ሳምንት ጨዋታ የጉልበት ጉዳት እንዳጋጠመው ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡
የ23 ዓመቱ ተጫዋች ጨዋታውን በቋሚነት…
በውጣ ውረድ የተገኘው ትልቁ ክብር – ኦስማን ዴምቤሌ…
አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኦስማን ዴምቤሌ ከበርካታ ውጣ ውረድ በኋላ ዳግም ከፍ ባለበት ፓሪስ የ2025 የባሎንዶር አሸናፊ በመሆን የወርቅ ኳሱን የግሉ አድርጓል።
ለዚህ ክብር የደረሰበት የእግር ኳስ መንገድ እንደ ብዙዎቹ የእግር ኳስ ከዋክብት የኦስማን ውጣ ውረድ የተለየው አልነበረም።
ዴምቤሌ በፈረንጆቹ 1997 ነበር በሰሜን ምዕራብ ፈረንሳይ…
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አዲስ አበባ ገባ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጃፓን ቶኪዮ በተካሄደው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል።
ልዑኩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ ሌሎች የስፖርት ዘርፍ…
ኦስማን ዴምቤሌ የባሎንዶር አሸናፊ ሆነ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የአጥቂ መስመር ተጫዋች ኦስማን ዴምቤሌ የ2025 ባሎንዶር ሽልማት አሸናፊ ሆኗል፡፡
የ2025 የባላንዶር አሸናፊ ሽልማት ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ በድምቀት ተካሂዷል፡፡
በዚህም ኦስማን ዴምቤሌ የባሎንዶር ሽልማትን ተቀዳጅቷል፡፡
ፍራንስ ፉትቦል በሚያዘጋጀው የባሎንዶር ሽልማት…
ከ34 ዓመታት በኋላ ያለ ወርቅ የተመለሰው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ…
አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጃፓን ቶኪዮ ሲካሄድ የቆየው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡
ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው ሁለት የብር እና ሁለት ነሐስ በድምሩ አራት ሜዳልያዎችን በማግኘት ውድድሩን አጠናቅቃለች።
ኢትዮጵያ ባገኘቸው የሜዳልያ ብዛት መሰረት አጠቃላይ ከተሳታፊ ሀገራት 21ኛ ደረጃ በመያዝ የቶኪዮ…