ስፓርት
ኢትዮጵያ መድን ሲዳማ ቡናን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ሲዳማ ቡናን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡
የኢትዮጵያ መድንን የማሸነፊያ ግቦች ወገኔ ገዛኸኝ፣ አቡበከር ሳኒ እና ብርሃኑ በቀለ (በራስ ላይ) ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድን ወደ ድል ሲመለስ ሲዳማ ቡና ከተከታታይ ሶስት ጨዋታዎች ድል በኋላ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ መድን በ63 ነጥብ ሊጉን ሲመራው ሲዳማ ቡና በ46 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡…
Read More...
ሊቨርፑል ድሉን ከደጋፊዎቹ ጋር እያከበረ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2024/25 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ድሉን ከደጋፊዎቹ ጋር እያከበረ ይገኛል።
የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል በአንፊልድ ጎዳናዎች ላይ በመዘዋወር ከደጋፊዎቹ ጋር 20ኛ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ድሉን እያከበረ ነው፡፡
በኮቪድ 19 ምክንያት ከአምስት ዓመት በፊት ሻምፒዮን ሆኖ…
የ2024/25 እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2024/25 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተደረጉ መርሐ ግብሮች ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡
ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ፣ ቼልሲ፣ አርሰናል እና ማንቼስተር ዩናይትድ ሲያሸንፉ የፕሪሚየር ሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል ከክሪስታል ፓላስ ጋር አቻ ተለያይቷል።
ውጤቱን ተከትሎም ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል በ84 ነጥብ ሲያጠናቅቅ፤…
ዴቪድ ራያ እና ማትዝ ሰልስ የወርቅ ጓንት አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርሰናል ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ እና የኖቲንግሃም ፎረስት ግብ ጠባቂ ማትዝ ሰልስ የ2024/25 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዘመንን የወርቅ ጓንት በጋራ አሸንፈዋል።
ሁለቱ ግብ ጠባቂዎች በውድድር ዓመቱ 13 ጊዜ መረባቸውን ሳያስደፍሩ በመውጣት ነው የወርቅ ጓንቱን ማሸነፍ የቻሉት።
ከብሬንት ፎርድ በውሰት…
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ይካሄዳሉ።
ሊቨርፑል አሸናፊነቱን አስቀድሞ ባረጋገጠበት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ38ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተመሳሳይ ሰዓት ምሽት 12፡00 ላይ ይደረጋሉ።
በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ከክሪስታል ፓላስ፣ ፉልሃም ከማቼስተር…
ሀድያ ሆሳዕና እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ31ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ሀድያ ሆሳዕናን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ ፀጋዓብ ይግዛው ሲያስቆጥር፤ አቤል ሀብታሙ የኢትዮ ኤሌክትሪክን የአቻነት ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ሀድያ ሆሳዕና ተከታታይ ሁለተኛ ጨዋታውን በአቻ ውጤት…
ሰንደርላንድ ዳግም ወደ ፕሪሚየር ሊግ አደገ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለማደግ በተደረገ የጥሎ ማለፍ የፍፃሜ ጨዋታ ሰንደርላንድ ሼፊልድ ዩናይትድን 2 ለ 1 በማሸነፍ ከሻምፒዮን ሺፕ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋጧል፡፡
ዌምብሌይ ስታዲየም ላይ በተደረገው የጥሎ ማለፍ የፍፃሜ ጨዋታ፤ ሰንደርላንድን ወደ ሊጉ ማሳደግ የቻሉትን ግቦች ማዬንዳ እና ቶም ዋትሰን…