ስፓርት
የአስቶን ቪላ እና ማንቼስተር ዩናይትድ ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 17ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ጨዋታ ዛሬ ቀጥሎ ሲካሄድ በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ የሚመራው አስቶን ቪላ ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል።
አስቶን ቪላ በውድድር ዓመቱ ድንቅ ብቃት በማስመልከት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በ33 ነጥብ ሶስተኛ ላይ ሲሆን ወጥ ብቃት ማሳየት የቸገረው ማንቼስተር ዩናይትድ በ26 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ማንቼስተር ዩናይትድ በጥሩ ቁመና ላይ ከሚገኘው እና በሜዳው ቪላ ፓርክ ከሚጫወተው አስቶን ቪላ ከባድ ፈተና እንደሚገጥመው ይጠበቃል።…
Read More...
15ኛው የምስራቅ አፍሪካ ካራቴ ሻምፒዮና በኢትዮጵያ የበላይነት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት የተካሄደው 15ኛው የምስራቅ አፍሪካ ካራቴ ሻምፒዮና በኢትዮጵያ የበላይነት ተጠናቅቋል።
በሻምፒዮናው ኢትዮጵያውያን ተወዳዳሪዎች በሲኒየር 6 እና በጁኒየር 6 በድምሩ 12 የወርቅ ሜዳሊያ አምጥተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በሲኒየር ውድድሮች 9 የብር እና 3 የነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል።
ሶማሊያ፣…
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ 33 ሜዳሊያ በማግኘት አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ በቆየው 4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ 33 ሜዳሊያዎችን በማግኘት አጠናቀቀች፡፡
የውድድሩ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን፥ ኢትዮጵያ በውድድሩ 8 ወርቅ፣ 9 የብር እና 16 የነሃስ በጥቅሉ 33 ሜዳልያዎችን አግኝታለች፡፡
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል የ2027ቱን…
ቼልሲ ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ከሜዳው ውጭ ኒውካስል ዩናይትድን የገጠመው ቼልሲ 2 ለ 2 አቻ ተለያይቷል፡፡
ባለሜዳው ኒውካስል በቮልትማደ ሁለት ግቦች 2 ለ 0 ሲመራ ቢቆይም፥ ቼልሲ በሪስ ጀምስ እና ዦአዎ ፔድሮ ግቦች ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ማንቼስተር ሲቲ…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ስምንት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ስምንት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ቼልሲ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ አቅንቶ ኒውካስል ዩናይትድን የሚገጥምበት የዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 9 ሰዓት ከ30 ይደረጋል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል…
በወርልድ ቴኳንዶ ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአንጎላ ሉዋንዳ እየተደረገ በሚገኘው 4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ በቴኳንዶ 73 ኪሎ ግራም ዮሐንስ ዘለቀ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አምጥቷል።
ዮሐንስ በፍፃሜ ጨዋታ ኮትዲቯራዊውን ተጋጣሚ በመርታት ነው የወርቅ ሜዳሊያ ያመጣው።
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ በ4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ ስምንተኛ የወርቅ…
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባ ምንጭ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ10ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባ ምንጭ ከተማን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች አዲስ ግደይ (2) እና ሳይመን ፒተር አስቆጥረዋል፡፡
አርባምንጭ…