ስፓርት
ደቡብ አፍሪካ ዚምባቡዌን በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ ዚምባቡዌን 3 ለ 2 አሸንፋለች፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የደቡብ አፍሪካን የማሸነፊያ ግቦች ሞሬሚ፣ ፎስተር እና አፖሊስ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
የዙምባቡዌን ግቦች ደግሞ ማስዋንሂሴ እና ሞዲባ (በራስ ላይ) አስቆጥረዋል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ግብጽ እና አንጎላ ያደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በምድብ ሁለት ከተደለደሉት መካከል ግብጽ እና ደቡብ አፍሪካ ጥሎ…
Read More...
መቐለ 70 እንደርታና ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ተመስገን ተስፋዬ የመቐለ 70 እንደርታን ግብ ሲያስቆጥር አቤል ያለው የቅዱስ ጊዮርጊስን ግብ…
አንቶኒ ጆሹዋ የመኪና አደጋ አጋጠመው
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብሪታኒያዊው አንቶኒ ጆሹዋ በናይጄሪያ የመኪና አደጋ ደርሶበታል፡፡
የቀድሞ የከባድ ሚዛን የዓለም ሻምፒዮን ቦክሰኛ አንቶኒ ጆሹዋ በናይጄሪያ ባጋጠመው የመኪና አደጋ መቁሰሉ ነው የተገለጸው፡፡
የ36 ዓመቱ ጆሹዋ በማኩን በሚገኘው ሌጎስ-ኢባዳን የፍጥነት መንገድ ላይ በመኪና እየተጓዘ ሳለ ከቆመ መኪና ጋር በመጋጨቱ ጉዳት…
ፋሲል ከነማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አንዋር ሙራድ አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ፋሲል ከነማ ነጥቡን ወደ 24 ከፍ በማድረግ ሊጉን መምራት ጀምሯል፡፡…
በአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በዛሬው ዕለት አራት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
በምድብ አንድ አዘጋጇ ሞሮኮ ከከዛምቢያ እንዲሁም ኮሞሮስ ከማሊ ምሽት 4 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ምድቡን ሞሮኮ በአራት ነጥብ እየመራች ሲሆን ማሊ እና ዛምቢያ በሁለት ነጥብ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃ…
ሱዳን ኢኳቶሪያል ጊኒን አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ ሱዳን ኢኳቶሪያል ጊኒን 1 ለ 0 አሸንፋለች።
በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ምሽት 12፡00 ላይ በተደረገው ጨዋታ የሱዳንን የማሸነፊያ ግብ ሳውል ኮኮ በራሱ መረብ ላይ አሳርፏል።
ቀደም ሲል ቀን 9፡30 ላይ በተደረገው ጨዋታ…
ሰንደርላንድ እና ሊድስ ዩናይትድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሰንደርላንድ እና ሊድስ ዩናይትድ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ዛሬ 11፡00 ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሳይሞን አዲንግራ የሰንደርላንድን ግብ ሲያስቆጥር ካልቨርት ሉዊን የሊድስ ዩናይትድን ግብ ከመረብ አገናኝቷል።
የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት…