ስፓርት
ሞዛንቢክ ጋቦንን አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ ሞዛንቦክ ጋቦንን 3 ለ 2 አሸንፋለች።
በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቀን 9፡30 ላይ በተደረገው ጨዋታ የሞዛንቢክን ግቦች ዲዮጎ ካሊላ፣ ጄኒ ካታሞ፣ ፋይሳል ባንጋል ሲያስቆጥሩ÷ ኦባሚያንግ እና ሙኬቱ ሙሳውንዳ የጋቦንን ግቦች አስቆጥረዋል።
የዛሬው መርሐ ግብር ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢኳቶሪያል ጊኒ ከሱዳን እንዲሁም ምሽት 2:30 ላይ አልጄሪያ ከቡርኪናፋሶ፤ ምሽት 5…
Read More...
በአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
በዕለቱ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 9 ሰዓት ከ30 ላይ ጋቦን እና ሞዛምቢክ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ደግሞ ኢኳቶሪያል ጊኒ ከሱዳን እንዲሁም…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ቀን 9 ሰዓት ከ30 ኖቲንግሃም ፎረስት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ሁለተኛ ላይ የተቀመጠውን ማንቼስተር ሲቲን ያስተናግዳል።
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ደግሞ የሊጉ መሪ አርሰናል በሜዳው ከብራይተን ጋር ሲጫወት ሊቨርፑል በተመሳሳይ ሰዓት በሊጉ…
በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በዛሬው ዕለት አራት የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ምሽት 5 ሰዓት ላይ በምድብ ሶስት የተደለደሉት ናይጄሪያና ቱኒዚያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ቡድኖቹ የምድብ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በድል መወጣታቸው ይታወሳል።
ከዚህ…
አንጎላ እና ዚምባቡዌ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ ዛሬ ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 9 ሰዓት የተገናኙት አንጎላ እና ዚምባቡዌ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ጄልሰን ዳላ ለአንጎላ እንዲሁም ኖሌጅ ሙሶና ለዚምባቡዌ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ጨዋታው ቀጥሎ ሲካሄድ ግብጽ እና ደቡብ አፍሪካ ምሽት 12…
መቻል አዳማ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ11ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መቻል አዳማ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቻልን ግቦች መሀመድ አበራ (2) እና በረከት ደስታ አስቆጥረዋል፡፡
አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ አህመድ ሁሴን ከመረብ አሳርፏል፡፡…
ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስል ዩናይትድ…
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስል ዩናይትድ ይጫወታሉ፡፡
ያለፉትን ተከታታይ ሁለት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻሉት ሁለቱም ክለቦች ወደ ድል ለመመለስ ዛሬ ምሽት 5 ሰዓት በኦልድትራፎርድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ሁለቱ ቡድኖች በፕሪሚየር ሊጉ እርስ…