ስፓርት
በሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ ቼልሲ ሊቨርፑልን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠባቂ ጨዋታ ቼልሲ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ምሽት 1፡30 ላይ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ሊቨርፑልን ያስተናገደው ቼልሲ ካሴዶ እና ኢስቲቫኦ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
የሊቨርፑልን ብቸኛ ግብ ጋክፖ አስቆጥሯል።
ቀን 11 ሰዓት ላይ በተካሄዱ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ሰንደርላንድን እንዲሁም አርሰናል ዌስትሀምን 2 ለ 0 በሆነ ተመሳሳይ…
Read More...
ቶተንሀም ሊድስ ዩናይትድን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቶተንሀም ሆትስፐር ሊድስ ዩናይትድን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ቀን ከ8:30 ላይ በሊድስ ሜዳ ኢላንድ ሮድ በተካሄደው ጨዋታ ቶተንሃም ድል ቀንቶታል።
በዚህም ፈረንሳዊው ማቲይስ ቴል እና ጋናዊው ሞሀመድ ኩዱስ የቶተንሀምን ግቦች አስቆጥረዋል።…
ቼልሲ ከሊቨርፑል – የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ7ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቼልሲ ከሊጉ መሪ ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ ካስተናገደው ሁለት ተከታታይ ሽንፈት መልስ ሊቨርፑልን በስታምፎርድ ብሪጅ የሚያስተናግድበት ጨዋታ ምሽት 1፡30 ይጀምራል፡፡
ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ቀን 11 ሰዓት ላይ አርሰናል በውጤት…
የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሳዳት ጀማል ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሳዳት ጀማል ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡
ሳዳት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በተለያዩ ክለቦች በግብ ጠባቂነት ተጫውቶ ያሳለፈ ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ በመሆን አገልግሏል፡፡
የቀድሞ ተጫዋችና አሰልጣኝ ሳዳት ጀማል በገጠመው ህመም…
ሪያል ማድሪድ ካይራት አልማቲን 5 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ የካዛኪስታኑን ክለብ ካይራት አልማቲን 5 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ45 በተደረገው ጨዋታ ፈረንሳዊው አጥቂ ኬሊያን ምባፔ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሲሰራ÷ ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና በራሂም ዲያዝ አስቆጥረዋል፡፡
በሌላ ጨዋታ…
ዊሊያም ሳሊባ በአርሰናል ውሉን አራዘመ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ በአርሰናል ለተጨማሪ አምስት አመታት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡
ሪያል ማድሪድ የ24 ዓመቱን ተጫዋች ለማስፈረም ጥብቅ ፍላጎት እንዳለው ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
ሆኖም ተጫዋቹ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በኢምሬትስ ለመቆየት የተስማማ ሲሆን፥ በመጪው ክረምት የሚያበቃውን ውሉን አድሷል፡፡…
ጆዜ ሞሪንሆን ከቀድሞ ክለባቸው ቼልሲ የሚያገናኘው የዛሬ ምሽት ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ2ኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች ይደረጋሉ፡፡
ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ቤኔፊካን እየመሩ በስታምፎርድ ብሪጅ የቀድሞ ክለባቸው ቼልሲን የሚገጥሙበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ፖርቹጋላዊ አሰልጣኝ ከምሽቱ ጨዋታ አስቀድሞ ስለ ቀድሞ ክለባቸው በሰጡት…