Fana: At a Speed of Life!

አቶ ማሞ ምህረቱ ከአሜሪካ ግምጃ ቤት ምክትል ረዳት ፀሐፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 26 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ከአሜሪካ ግምጃ ቤት ምክትል ረዳት ፀሐፊ ኤሪክ ሜየር ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር ላይ ያተኮረ መሆኑን ባንኩ በትዊተር ገጹ ባሰፈረው መረጃ አመላክቷል።

የባንኩ ገዥ የአሜሪካ ግምጃ ቤት በኢትዮጵያ እድገትን ለማፋጠን እና የኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲመጣ እየተወጣ ላለው ገንቢ ሚና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.