Fana: At a Speed of Life!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 90 የተለያዩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ናቸው – ቢሮው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በክልሉ 90 የተለያዩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ናቸው አለ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል ፕሮጀክቶቹ በ”አንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት” በሚል ኢኒሼቲቭ እየተሰሩ መሆናቸውን ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።

በዚህም 18 የፐብሊክ ፋርማሲ፣ 10 የጤና ተቋማት፣ 10 የትምህርት ቤት ግንባታዎች፣ 10 የከተማ መብራት ዝርጋታዎች፣ ሰባት የውሃ መስመር ዝርጋታዎች እና ሌሎች ተመሳሳይ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እንደሆኑ አብራርተዋል፡፡

የፕሮጀክቶቹ ግንባታ በ2 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር መነሻ ወጪ እየተከናወኑ እንደሆነ ገልጸው÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዓመቱ የመጀመሪያ ዙር የአመራር ስልጠና መድረክ ላይ በሰጡት አቅጣጫ መሠረት እየተሰሩ ስለመሆናቸውም አመልክተዋል።

ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ስንታየሁ ገልጸዋል፡፡

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.