Fana: At a Speed of Life!

በተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በማንሰራራት ላይ ይገኛል – ፕሬዚዳንት ታዬ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ተግባራዊ በተደረገው የማክሮ ኦኮኖሚ ማሻሻያ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በማንሰራራት ላይ ይገኛል አሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፡፡ 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤትና የፌዴሬሽን ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን…

ቢሾፍቱ የሀርሰዴ ኢሬቻ በዓልን ለማክበር ዝግጅት አድርጋ እንግዶችን ተቀብላለች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሠፋ የሀርሰዴ ኢሬቻ በዓልን ለማክበር አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገን እንግዶችን ተቀብለናል አሉ። የቢሾፍቱ ከተማ ዘንድሮ በኮሪደር ልማት ተውባ እንግዶቿን በደማቅ ሁኔታ ተቀብላለች። የዘንድሮ…

የምክክር ኮሚሽን በተለያዩ አውሮፓ ሀገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አጀንዳዎችን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በስዊዲን፣ በኖርዲክ እና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተለዩ አጀንዳዎችን ተረክቧል፡፡ ኮሚሽኑ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ከሚኖሩ…

በሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ ቼልሲ ሊቨርፑልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠባቂ ጨዋታ ቼልሲ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ። ምሽት 1፡30 ላይ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ሊቨርፑልን ያስተናገደው ቼልሲ ካሴዶ እና…

የሕክምና አገልግሎት ጥራትን በማሳደግ አምራች ዜጋ የማፍራት ተግባራት ይጠናከራል – እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት በማሳደግ ጤናማና አምራች ዜጋ የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል አሉ። ‘በባለቤትነት ላይ የተመሰረተ ዕውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ…

የልማት ስራዎች መዲናዋን የስበት ማዕከል አድርገዋታል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ የተሰሩ የልማት ስራዎች ከተማዋን የስበት ማዕከል አድርጓታል አሉ። አዲስ አበባ የአደባባይ በዓሎችንና ትላልቅ ኹነቶችን የማስተናገድ አቅሟን እንዲሁም መስተንግዶዋ ዓለም አቀፋዊ…

የጢያ ዓለም አቀፍ መካነ ቅርስን በማልማት የገቢ ምንጭ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የጢያ ዓለም አቀፍ መካነ ቅርስን በማልማትና የገቢ ምንጭ በማድረግ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል አሉ። በክልሉ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ…

የኢንቨስትመንት ፍቃድ የወሰዱ አልሚዎች የስራ እንቅስቃሴን በጥብቅ ዲሲፕሊን መምራት ይገባል – አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንቨስትመንት ፍቃድ የወሰዱ አልሚዎች የስራ እንቅስቃሴን በጥብቅ ዲሲፕሊን መምራት ይገባል አሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ። የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ የኢንቨስትመንት ማዕድንና ኢነርጂ ፅ/ቤት አንደኛ ሩብ ዓመት…

ቶተንሀም ሊድስ ዩናይትድን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቶተንሀም ሆትስፐር ሊድስ ዩናይትድን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ። ቀን ከ8:30 ላይ በሊድስ ሜዳ ኢላንድ ሮድ በተካሄደው ጨዋታ ቶተንሃም ድል ቀንቶታል። በዚህም…

ሴቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ለሀገራዊ ምክክር ስኬት ወሳኝ ሚና አላቸው – መስፍን አረዓያ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አረዓያ (ፕ/ር) ሴቶች፣ ወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ወሳኝ ሚና አላቸው አሉ። ኮሚሽኑ ‘የሴቶች፣ ወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች ሚና ለሀገራዊ ምክክር…