Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ እየተሰራ ነው ተባለ 

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና በድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና ኢንቨስት እንዲያደርጉ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ በዱባይና ሰሜን ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ቆንስል ጄኔራል አምባሳደር አክሊሉ ከበደ ገለፁ። አምባሳደር…

የግብርና ምርት አቅራቢ አርሶ አደሮችን ከሸማቾች ጋር የሚያገናኝ መተግበሪያ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የአርሶ አደሮችን ምርታማነት ማሳደግ የሚያስችሉ ሁለት መተግበሪያዎችን ይፋ አድርጓል። መተግበሪያዎቹ ዲጂታል ማርኬት ሊንኬጁ እና አውቶሜሽን ኢንፑት ቮቸር (ኢ_ቮቸር 2.0) የተሰኙ ናቸው። ዲጂታል…

የባሕር ዳር ከተማ የሕዝባዊ የሰላም ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መድረክ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር በሁሉም ክፍለ ከተሞች "ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሀሳብ ሲካሄድ የነበረው ሕዝባዊ የሰላም ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ…

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምዕራብ ሸዋ ዞን የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ አመራሮች በምዕራብ ሸዋ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም በአምቦ ከተማ በመከናወን ላይ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን መመልከታቸው…

በትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ አሥተዳደር ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ ሌሊት 6፡30 ገደማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ ከሟቾች በተጨማሪም በ10 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የድሬዳዋ አሥተዳደር ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡ አደጋው…

የተፈጥሮ ሣይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተፈጥሮ ሣይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው እየተሰጠ የሚገኘው በወረቀት እና በበይ መረብ ሲሆን÷ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚቆይም ተገልጿል፡፡ የማኅበራዊ…

አምባሳደር ታዬ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ የጋራ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡ በተለይም ሁለቱ ወገኖች በሱዳን የሰላም…

1 ሺህ 198 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 198 ኢትዮጵያውያን በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ተመላሾቹ 1ሺህ 041 ወንዶች፣ 134 ሴቶች እና 23 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ ÷ ከእነዚህ መካከልም 31 እድሜያቸው ከ11 ዓመት በታች የሆኑ…

ሉዊስ ናኒ እና ንዋንኩ ካኑ ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሉዊስ ናኒ እና ንዋንኩ ካኑ ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ከውይይቱ በኋላም ሉዊስ ናኒ ከሀገሩ ፖርቹጋል ማሊያ ላይ ፊርማውን አኑሮ ለፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በስጦታ አበርክቷል። በሌላ…

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚካሂል ቦግዳኖቭን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሀገራዊ፣ቀጠናዊ እና አህጉራዊ የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡ ሁለቱ ወገኖች በሀገራቱ…