Browsing Category
ዓለምአቀፋዊ ዜና
የቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካሃን የ3 ዓመት እስር ተፈረደባቸው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካሃን ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ የሦስት ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቢሯቸው ውስጥ የተቀበሏቸውን ስጦታዎች በመሸጥ የተገኘውን ገንዘብ ባለማሳወቃቸው ጥፋተኛ ተብለው ውሳኔው…
ዩክሬን በምዕራባውያን የጦር ታክቲኮች ተስፋ ቆርጣለች – ኒዮርክ ታይምስ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 27 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዩክሬን የሩሲያን ጦር ለመመከት ምዕራባውያን ባሳዩዋቸው የጦር ታክቲኮች ተስፋ ቆርጣለች ሲል የአሜሪካው ኒዮርክ ታይምስ ጋዜጣ አስነብቧል፡፡
ኒዮርክ ታይምስ እንደዘገበው÷ በኔቶ የተሳሳተ የጦር እቅድ ምክንያት ዩክሬን ከባድ ወታደራዊ ኪሳራ…
የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትሮች ለዘላቂ ቱሪዝም ልማት እንዲሰሩ ጋና ጥሪ አቀረበች
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትሮች ለአህጉሩ ዘላቂ ቱሪዝም ልማት እንዲሰሩ የጋና ቱሪዝም፣ ኪነ-ጥበብና ባህል ሚኒስትር ኢብራሂም መሀመድ አዋል (ዶ/ር) ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትሮች አካባቢን ለመጠበቅ እና…
በቤጂንግ በ140 ዓመታት ታሪክ ውስጥ አጋጥሞ የማያውቅ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ጣለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና ቤጂንግ ከፈረንጆቹ ሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 2 ቀን 2023 በ140 ዓመታት ታሪክ ውስጥ አጋጥሞ የማያውቅ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ መጣሉ ተገለጸ።
ከተማዋ በቅዳሜ እና ረቡዕ ጠዋት መካከል 744 ነጥብ 8 ሚሊ ሜትር ዝናብ መመዝገቡን…
የደቡብ አሜሪካ ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳላቸው ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ አሜሪካ ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳላቸው ተገለጸ፡፡
ወደ ብሪክስ የኢኮኖሚ ቡድን ለመግባት ዝግጁ የሆኑት ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ቦሊቪያ እንደተካተተች የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮሄልዮ ማይታ ተናግረዋል።
በደቡብ…
የኒውክሌር ጦርነት ከአየር ንብረት ለውጥ የከፋ አይደለም -አንቶኒ ብሊንከን
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኒውክሌር ጦርነት ከአየር ንብረት ለውጥ የከፋ አይደለም ሲሉ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ገለፁ፡፡
ሚኒስትሩ በትናንትናው እለት በአውስትራሊያው 60 ደቂቃ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ እንደተናገሩት÷ በዓለም እየተስተዋለ የመጣው…
ሳውዲ አረቢያ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ወታደራዊ ግጭቱን እንዲያቆሙ ጥሪ አቀረበች
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሳውዲ አረቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፋይሰል ቢን ፋርሃን አል ሳኡድ በሱዳን ውስጥ የሚፋለሙ ወገኖች ሁሉንም አይነት ወታደራዊ ፍጥጫ በማቆም ሀገሪቱን ወደ መረጋጋት መመለስ የሚያስችል ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈልጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ከሱዳን…
ፕሬዚዳንት ፑቲን የአፍሪካ የሰላም ሐሳብ ለሩሲያ-ዩክሬን ሰላም መሰረት ሊሆን ይችላል አሉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ፑቲን በአፍሪካ መሪዎች የቀረበው የሰላም ሐሳብ በሩሲያ-ዩክሬን የሚካሄደውን ጦርነት ለማስቆም የሰላም መሰረት ሊሆን እንደሚችል ገለጹ፡፡
ሬውተርስን ጠቅሶ አልጄዚራ እንደዘገበው÷ የአፍሪካ መሪዎች ያቀረቡት የሰላም ዕቅድ ምንም እንኳን ሙሉ…
አሜሪካ ለታይዋን የ345ሚሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ይፋ አደረገች
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ ለታይዋን የ345 ሚሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ይፋ አድርጋለች፡፡
ድጋፉ ታይዋን ከየትኛውም አካል ሊቃጣ የሚችልን ትንኮሳ በራሷ አቅም ለመከላከል የምታደርገውን ጥረት እንደሚያሳድግ ተመላክቷል፡፡
የድጋፍ ማዕቀፉ የአየር መቃወሚያ፣…
በአፍሪካ እና በሩሲያ መካከል ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ተስማምተናል – ፕሬዚዳንት ፑቲን
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ሀገራት እና ሩሲያ መካከል ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ስምምነት ላይ ደርሰናል ሲሉ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ገለፁ።
ፕሬዚዳንቱ ሩሲያ እና አፍሪካ ትብብራቸውን በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በቴክኖሎጂ፣ በመሰረተ ልማት ግንባታ፣…